20110819

“ድንግል ማርያም ” ነኝ ባይዋ ሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው

“ የሥላሴ መንፈስ በእኔ ላይ አድሯል፣ ከእግዚአብሔር የተላክሁ ማርያም ነኝ” በሚል ድንኳን በመኖሪያ ቤቷ አካባቢ ተክላ ተከታዮች ስታፈራና እምነቷን ስታስፋፋ የነበረችው ሴት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተካሄደባት ነው፡፡

በአምቦ ከተማ ገላን በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ተወልዳ በ1994 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ትዕግስት ብርሃኑ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ “ማርያም ነኝ” በሚል ማሳሳቻ ተከታዮችን አፍርታ እንደነበር ከፖሊስ የተገኘ ማስረጃ ይጠቁማል፡፡

በዚሁ አመት የፋሲካ በዓል ሰሞን “እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቼ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ” በማለት ዝግጅት የጀመረችው ትዕግስት፣ የስቅለት ዕለት የሾህ አክሊልና የምትሰቀልበትን መስቀል አዘጋጅታ ጀርባዋን እንደ ተገረፈች ታውቋል፡፡

በመስቀሉ ላይ መሰቀሏን ያየ ግን አልተገኘም፡፡ በሦስተኛው ቀን ትዕግስት ከሞት ተነሳች ተብሎ ለአካባቢው ህዝብ እንደታየች ምንጮች ይናገራሉ፡፡ የት ደርሳ እንደመጣች የጠየቃት ስለመኖሩ ግን የታወቀ ነገር የለም፡፡ አብረዋት ይኖሩ የነበሩት አባቷ አቶ ብርሃኑ ድርጊቷን አጥብቀው ይቃወሙ እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች ጠጥተው ቤት ሲገቡ በጉዳዩ ይነታረኩ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ አባቷ ግን የልጃቸውን መለኮታዊ ነኝ ባይነት ማስቆም አልቻሉም፡፡ ትዕግስት ይባሱኑ “የሥላሴ መልዕክተኛ ድንግል ማርያም ነኝ” ማለት ጀመረች ይላሉ- ምንጮች፡፡

በዚህ አድሯጎቷ የአካባቢው ነዋሪ ህዝብ ተቃውሞውን በማሰማት ከአካባቢው አባረራት፡፡ ትዕግስት በዚህ ጊዜ ወንጪ ገዳም እንደገባች የገለፀው ፖሊስ፣ ሀይለገብርዔል ከተባለው ተከታይዋ ሦስተኛ ልጇን እንደወለደች ይናገራል፡፡ ከወንድ ጋር ተገናኝታ እንደማታውቅ የምትናገረው ትዕግስት፣ ሦስቱንም ልጆቼን በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው ባይ ናት፡፡ የመጀመሪያ ባለቤቷም ይሄንኑ ይመሰክራል- ከእሷ ጋር ስጋዊ ግንኙነት ፈፅሞ እንደማያውቅና ሁለት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ እንደወለደቻቸው በመናገር፡፡

ትዕግስት በወንጭ ገዳም ሳለች የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ ማለቷን- ገፍታ ቀጠለችበት፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌላ ጉድ መከሰቱን የሚናገሩ ምንጮች፣ እናቷ ወይዘሮ ባይሴ ኡዊሳ (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) ነሐሴ 25/2000 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት ሞተው እንደተገነዙ፣ ከዚያም የዚያኑ ዕለት ከምሽቱ 4 ሰዓት ከሞት ተነሱ ተብሎ እንደተዋራ ይናገራሉ፡፡ እናት ከሞት የተነሱት ከሰማይ የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ እንደሆነ ገልፀው “ወ/ሮ ትዕግስት ወይም በክርስትና ስሟ ምስለ ፍቅር ኢየሱስን ስሟት ተብላችኋል” ካሉ በኋላ በነጋታው ተመልሰው እንደሞቱና ነሐሴ 27/2000 የቀብራቸው ሥነስርዓት እንደተፈፀመ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ግን መቃብራቸው ተከፍቶ እንዳረጉ ነው ልጃቸው ትዕግስት የተናገረችው፡፡

ነሐሴ 29/2000 ዓ.ም ሌሊት ላይ ነጎድጓድ መብረቅ ሰምቶ ከጥበቃ ክፍሉ እንደወጣ የሚናገረው የገዳሙ የጥበቃ ሰራተኛ፣ የትዕግስት እናት መቃብር ላይ መላዕክት እንዳየ ለፖሊስ ገልጿል፡፡ በእጁ አብርቶ ይዞት የነበረው ባትሪ መጥፋቱንና መብረቁ ገፍትሮ እንደጣለው ለፖሊስ የገለፀው የጥበቃ ሠራተኛ በድንጋጤ ወደክፍሉ ተመልሶ እንደገባ ተናግሯል፡፡ ሲነጋጋ ሁኔታውን ለማጣራት ወደ መቃብሩ ሲሄድ የወለተ ሥላሴ መቃብር ለሁለት ተከፍሎና መሃሉ ተሰንጥቆ፣ የአስከሬን ሳጥኑ ባዶ ሆኖ ማየቱን በሰጠው ቃል ገልጿል፡፡

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ትዕግስት “የዓለም ፍፃሜ ደርሷል፣ ንስሃ ግቡ” እያለች መስበክ መጀመሯን ምንጮች ይናገራሉ፡፡

ሴትየዋ የተቀበሩበት ስፍራ ታጥሮ በሰዎች እየተጎበኘ እንደሆነ የጠቆመው ፖሊስ፣ ሁኔታው የማጣራት ስራ እንደሚፈልግም ይናገራል፡፡

በረቡዕ ቀን በሬና በግ አርዳ ነዋሪዎች በፆም ቀን ሥጋ እንዲበሉ ማስገደዷ ከነዋሪው ጋር ለተፈጠረው ግጭት መንስኤ ሲሆን፣ የፆም ቀን ቢሆንም አብርሃም ቤትም በሬ ተጥሎ ለሰዎች የመገበው ሐምሌ ሰባት እንደሆነ በመፅሃፍ ቅዱስ ተፅፏል በማለት ሐምሌ 7/2002 ዓ.ም ነዋሪው ሥጋ እንዲበላ፣ ካልበሉ ግን ምድር ተከፍታ እንደምትውጣቸው ታስፈራራ ነበር ተብሏል፡፡

ሥጋውን የበላ ይማራል በማለቷ ግማሹ ነዋሪ ቢበላም ግማሹ አልበላም እንዳለ የጠቆሙ ምንጮች፣ በዚህም ምክንያት ትግስት ከአካባቢው ለቅቃ አዲስ አበባ እንደገባች ይናገራሉ፡፡

አዲስ አበባ ከተከታዮቿ አንዷ በሆነችው ሃና ብሩክ በተባለች ግለሰብ መኖሪያ ቤት (ሳር ቤት አካባቢ) ያረፈችው ትዕግስት፣ ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 16 ህፃናትና ጎልማሶች አብረዋት ይኖሩ እንደነበር ታውቋል፡፡ ህፃናቱን ለልመና ተግባር ትጠቀምባቸው እንደነበር የጠቆመው ፖሊስ ፣ እሷን ተከታይ እንደሆኑና ደረታቸውን በድንጋይ እንዲደለቁ ታደርጋቸው እነደነበር እንዳረጋገጠ አመልክቷል፡፡

አብዛኞቹ ተከታዮቿ ራሳቸውን የማያውቁና ከትክክለኛ አእምሯቸው እንደተለዩ የሚናገረው ፖሊስ፣ የሴትየዋ ድርጊት የተጋለጠው ህፃናቱ ለጎረቤት “እመብርሃን ናት፣ ደሟን እየቀዳች የክርስቶስ ደም ነው እያለች ታጠጣናለች” ብለው ከተናገሩ በኋላ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመጠቆም ወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ በቁጥጥር ስር እንደዋለች ገልጿል፡፡

በወቅቱ ፍተሻ አለመካሄዱን የጠቆመው ፖሊስ፣ ህፃናቱ የት እንዳሉ እንደማያውቅና ምርመራ ላይ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከሦስት ዓመት በፊት ከተከታዮቿ አንዷ የነበረችው የ19 አመቷ ትዕግስት ያለው ለስምንት ቀን ያለምግብ በመቆየቷ፣ ደረቷን በድንጋይ እንድትደልቅና የተበጠበጠ ምንነቱ ያልታወቀ ቅጠል እንድትጠጣ በመደረጉ ህይወቷ እንዳለፈ ገልጿል፡፡ የወጣቷን አስከሬን በማውጣት የአማሟቷን ሁኔታ ለማጣራት ከህክምና ባለሙያዎች ጋር አየተመካከረ እንደሆነም ፖሊስ አክሎ ገልጿል፡፡

ከወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ ጋር በተያያዘ ትዳራቸው የፈረሰ፣ ንብረታቸውን ያጡ ግለሰቦች እንዳሉም የፖሊስ መረጃ ይጠቁማል፡፡

አዲስ አበባ ቤቴል የተባለው ሰፈር ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አለሚቱ በትዕግስት በደል እንደደረሰባት ቃሏን ለፖሊስ ሰጥታለች፡፡ ቤተሰቦቿ ወደ አምቦ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጉደር ከተማ የወሰዷት፣ ወ/ሮ ትዕግስት በፀበል ከህመምሽ ትፈውስሻለች በሚል እንደሆነ የተናገረችው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ከተጠመቀች በኋላ ከቲቢ ካንሰር ተፈውሰሻል ብለው ህዝብ ተሰብስቦ በቪዲዮ እንደተቀረፀች ለፖሊስ ገልፃለች፡፡

ከዚህም በኋላ ደግሞ ልጆቼንና ወርቄን ነጥቃኛለች የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ልጆችሽ የእኔ እንጂ የአንቺ አይደሉም መቧሏን ትናገራለች፡፡ “ አንድ ቀን የትንሿን ልጄን ፀጉር ሳበጥር ለምን ነካሻት ተብዬ እስከምዝለፈለፍ ድረስ ተደብድቤያለውሁ” ትላለች፡፡

ከእኔ የትም አታመልጡም ስለምትል ሁሉም ይፈራታል የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ተከታዮቿ “ እመቤታችን ናት አምልኳት” እንደሚሉ ትናገራለች፡፡ “በምስል ታመልካላችሁ፤ ይሄው በአካል መጥታለች አምልኳት” ይሉናል ብላለች፡፡ በየቀኑ ፆም አለ፣ በቀን አንዴ ንፍሮ እንበላለን ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ፆሙ የአዋቂ ብቻ ሳይሆን ከስድስት ወር ጀምሮ ያለ ህፃንም እንዲፆም ይደረጋል- ለሦስት ቀን ጡት አይሰጠውም ብላለች፡፡

ወ/ሮ ትዕግስት ትምህርት ሃጢያት ነው በሚል አቋም ልጆች እንዳይማሩ እንደምታደርግም ተበዳይዋ ለፖሊስ ተናግራለች፡፡ የ12 ዓመት ልጄን ከዚህ እንግልት ለማዳን እንጥፋ ብዬው ነበር ፣ እሱ ግን ፈርቶ እምቢ አለኝ የምትለው- አለሚቱ፣ የባሰው መከራ የመጣው ግን የ3 አመት ልጄ ለ3 ቀን ያለ እህል ውሃ ፆም ፀሎት መያዝ አለበት ስትላት እንደሆነ ተናግራለች፡፡ ትልቁ ልጄ አሻፈረኝ ስላለ ሌላ ሙከራ ባደርግ ይገሉኛል ብዬ ትንሿን ልጄን ይዤ ጠፋሁ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ የወንድ ልጇ ነገር ስላላስቻላት ተመልሳ ወደ አምቦ መሄዷን ትናገራለች፡፡

ሆኖም ሰው ሁሉ ስለጠላቸው ወደ አዲስ አበባ ሄደዋል ተብላ መመለሷንና ልጇን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማግኘቷን ገልፃ ለሳምንት ያህል አብሯት ከቆየ በኋላ እንደጠፋ ገልጻለች፡፡ ፖሊስ ልጇን ለሁለተኛ ጊዜ አግኝቶ የሰጣት ቢሆንም ተስማምተው ሊኖሩ እንዳልቻሉ እናት ትናገራለች፡፡ እኔን እንደ እናቱ ሳይሆን እንደ ጠላት ነው የሚያየኝ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ “ ማርያምን ከሰሻት እኔ ካንቺ ጋር አልኖርም” ይላት እንደነበር ገልፃለች፡፡ ልጄ “ እኛ ምድራዊ አይደለንም፣ ሰማያዊ ነን” እያለ እሷ የምትናገረውን ሲደግም ነገሩ ከአቅሜ በላይ እንደሆነ ስለገባኝ ወደ እነሱ እንዳይመለስ በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ተደርጓል የምትለው እናቱ አሁን ትንሽ ቢሻሻልም፣ እሷን ግን እንደጠላት እንደሚመለከታት ትናገራለች፡፡ ልጄ ጤነኛ አይደለም ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ንብረቴን በሙሉ አጥቼአለሁ ከምንም በላይ የሚፀፅተኝ ግን ልጄን ማጣቴ ነው ብላለች- እንባዋን እያፈሰሰች፡፡

ወ/ሮ ትዕግስት አበራ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ ስትሆን ጉዳይዋ ወደ ፍርድ ቤት ተልኮ በጊዜ ቀጠሮ ላይ ነው፡፡ ወ/ሮ ትዕግስት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል “ የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ እኔ ከወንድ ጋር አልተኛሁም፤ ተርፌሳም፣ ማርያምን ዮሴፍ ይጠብቃት እንደነበር ጠባቂዬ ነው፡፡ ሦስት ልጆች ቢኖሩኝም በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው፣ ይህንን ሁሉ ያደረኩት ሥላሴዎች አዘውኝ ነው፣ አላጠፋሁም” ብላለች፡፡

ምንጭ (ሳምንታዊው አዲስ አድማስ ጋዜጣ -ሰላም ገረመው)

“ድንግል ማርያም ” ነኝ ባይዋ ሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው

“ የሥላሴ መንፈስ በእኔ ላይ አድሯል፣ ከእግዚአብሔር የተላክሁ ማርያም ነኝ” በሚል ድንኳን በመኖሪያ ቤቷ አካባቢ ተክላ ተከታዮች ስታፈራና እምነቷን ስታስፋፋ የነበረችው ሴት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተካሄደባት ነው፡፡

በአምቦ ከተማ ገላን በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ተወልዳ በ1994 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ትዕግስት ብርሃኑ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ “ማርያም ነኝ” በሚል ማሳሳቻ ተከታዮችን አፍርታ እንደነበር ከፖሊስ የተገኘ ማስረጃ ይጠቁማል፡፡

በዚሁ አመት የፋሲካ በዓል ሰሞን “እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቼ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ” በማለት ዝግጅት የጀመረችው ትዕግስት፣ የስቅለት ዕለት የሾህ አክሊልና የምትሰቀልበትን መስቀል አዘጋጅታ ጀርባዋን እንደ ተገረፈች ታውቋል፡፡

በመስቀሉ ላይ መሰቀሏን ያየ ግን አልተገኘም፡፡ በሦስተኛው ቀን ትዕግስት ከሞት ተነሳች ተብሎ ለአካባቢው ህዝብ እንደታየች ምንጮች ይናገራሉ፡፡ የት ደርሳ እንደመጣች የጠየቃት ስለመኖሩ ግን የታወቀ ነገር የለም፡፡ አብረዋት ይኖሩ የነበሩት አባቷ አቶ ብርሃኑ ድርጊቷን አጥብቀው ይቃወሙ እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች ጠጥተው ቤት ሲገቡ በጉዳዩ ይነታረኩ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ አባቷ ግን የልጃቸውን መለኮታዊ ነኝ ባይነት ማስቆም አልቻሉም፡፡ ትዕግስት ይባሱኑ “የሥላሴ መልዕክተኛ ድንግል ማርያም ነኝ” ማለት ጀመረች ይላሉ- ምንጮች፡፡

በዚህ አድሯጎቷ የአካባቢው ነዋሪ ህዝብ ተቃውሞውን በማሰማት ከአካባቢው አባረራት፡፡ ትዕግስት በዚህ ጊዜ ወንጪ ገዳም እንደገባች የገለፀው ፖሊስ፣ ሀይለገብርዔል ከተባለው ተከታይዋ ሦስተኛ ልጇን እንደወለደች ይናገራል፡፡ ከወንድ ጋር ተገናኝታ እንደማታውቅ የምትናገረው ትዕግስት፣ ሦስቱንም ልጆቼን በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው ባይ ናት፡፡ የመጀመሪያ ባለቤቷም ይሄንኑ ይመሰክራል- ከእሷ ጋር ስጋዊ ግንኙነት ፈፅሞ እንደማያውቅና ሁለት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ እንደወለደቻቸው በመናገር፡፡

ትዕግስት በወንጭ ገዳም ሳለች የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ ማለቷን- ገፍታ ቀጠለችበት፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌላ ጉድ መከሰቱን የሚናገሩ ምንጮች፣ እናቷ ወይዘሮ ባይሴ ኡዊሳ (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) ነሐሴ 25/2000 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት ሞተው እንደተገነዙ፣ ከዚያም የዚያኑ ዕለት ከምሽቱ 4 ሰዓት ከሞት ተነሱ ተብሎ እንደተዋራ ይናገራሉ፡፡ እናት ከሞት የተነሱት ከሰማይ የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ እንደሆነ ገልፀው “ወ/ሮ ትዕግስት ወይም በክርስትና ስሟ ምስለ ፍቅር ኢየሱስን ስሟት ተብላችኋል” ካሉ በኋላ በነጋታው ተመልሰው እንደሞቱና ነሐሴ 27/2000 የቀብራቸው ሥነስርዓት እንደተፈፀመ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ግን መቃብራቸው ተከፍቶ እንዳረጉ ነው ልጃቸው ትዕግስት የተናገረችው፡፡

ነሐሴ 29/2000 ዓ.ም ሌሊት ላይ ነጎድጓድ መብረቅ ሰምቶ ከጥበቃ ክፍሉ እንደወጣ የሚናገረው የገዳሙ የጥበቃ ሰራተኛ፣ የትዕግስት እናት መቃብር ላይ መላዕክት እንዳየ ለፖሊስ ገልጿል፡፡ በእጁ አብርቶ ይዞት የነበረው ባትሪ መጥፋቱንና መብረቁ ገፍትሮ እንደጣለው ለፖሊስ የገለፀው የጥበቃ ሠራተኛ በድንጋጤ ወደክፍሉ ተመልሶ እንደገባ ተናግሯል፡፡ ሲነጋጋ ሁኔታውን ለማጣራት ወደ መቃብሩ ሲሄድ የወለተ ሥላሴ መቃብር ለሁለት ተከፍሎና መሃሉ ተሰንጥቆ፣ የአስከሬን ሳጥኑ ባዶ ሆኖ ማየቱን በሰጠው ቃል ገልጿል፡፡

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ትዕግስት “የዓለም ፍፃሜ ደርሷል፣ ንስሃ ግቡ” እያለች መስበክ መጀመሯን ምንጮች ይናገራሉ፡፡

ሴትየዋ የተቀበሩበት ስፍራ ታጥሮ በሰዎች እየተጎበኘ እንደሆነ የጠቆመው ፖሊስ፣ ሁኔታው የማጣራት ስራ እንደሚፈልግም ይናገራል፡፡

በረቡዕ ቀን በሬና በግ አርዳ ነዋሪዎች በፆም ቀን ሥጋ እንዲበሉ ማስገደዷ ከነዋሪው ጋር ለተፈጠረው ግጭት መንስኤ ሲሆን፣ የፆም ቀን ቢሆንም አብርሃም ቤትም በሬ ተጥሎ ለሰዎች የመገበው ሐምሌ ሰባት እንደሆነ በመፅሃፍ ቅዱስ ተፅፏል በማለት ሐምሌ 7/2002 ዓ.ም ነዋሪው ሥጋ እንዲበላ፣ ካልበሉ ግን ምድር ተከፍታ እንደምትውጣቸው ታስፈራራ ነበር ተብሏል፡፡

ሥጋውን የበላ ይማራል በማለቷ ግማሹ ነዋሪ ቢበላም ግማሹ አልበላም እንዳለ የጠቆሙ ምንጮች፣ በዚህም ምክንያት ትግስት ከአካባቢው ለቅቃ አዲስ አበባ እንደገባች ይናገራሉ፡፡

አዲስ አበባ ከተከታዮቿ አንዷ በሆነችው ሃና ብሩክ በተባለች ግለሰብ መኖሪያ ቤት (ሳር ቤት አካባቢ) ያረፈችው ትዕግስት፣ ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 16 ህፃናትና ጎልማሶች አብረዋት ይኖሩ እንደነበር ታውቋል፡፡ ህፃናቱን ለልመና ተግባር ትጠቀምባቸው እንደነበር የጠቆመው ፖሊስ ፣ እሷን ተከታይ እንደሆኑና ደረታቸውን በድንጋይ እንዲደለቁ ታደርጋቸው እነደነበር እንዳረጋገጠ አመልክቷል፡፡

አብዛኞቹ ተከታዮቿ ራሳቸውን የማያውቁና ከትክክለኛ አእምሯቸው እንደተለዩ የሚናገረው ፖሊስ፣ የሴትየዋ ድርጊት የተጋለጠው ህፃናቱ ለጎረቤት “እመብርሃን ናት፣ ደሟን እየቀዳች የክርስቶስ ደም ነው እያለች ታጠጣናለች” ብለው ከተናገሩ በኋላ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመጠቆም ወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ በቁጥጥር ስር እንደዋለች ገልጿል፡፡

በወቅቱ ፍተሻ አለመካሄዱን የጠቆመው ፖሊስ፣ ህፃናቱ የት እንዳሉ እንደማያውቅና ምርመራ ላይ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከሦስት ዓመት በፊት ከተከታዮቿ አንዷ የነበረችው የ19 አመቷ ትዕግስት ያለው ለስምንት ቀን ያለምግብ በመቆየቷ፣ ደረቷን በድንጋይ እንድትደልቅና የተበጠበጠ ምንነቱ ያልታወቀ ቅጠል እንድትጠጣ በመደረጉ ህይወቷ እንዳለፈ ገልጿል፡፡ የወጣቷን አስከሬን በማውጣት የአማሟቷን ሁኔታ ለማጣራት ከህክምና ባለሙያዎች ጋር አየተመካከረ እንደሆነም ፖሊስ አክሎ ገልጿል፡፡

ከወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ ጋር በተያያዘ ትዳራቸው የፈረሰ፣ ንብረታቸውን ያጡ ግለሰቦች እንዳሉም የፖሊስ መረጃ ይጠቁማል፡፡

አዲስ አበባ ቤቴል የተባለው ሰፈር ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አለሚቱ በትዕግስት በደል እንደደረሰባት ቃሏን ለፖሊስ ሰጥታለች፡፡ ቤተሰቦቿ ወደ አምቦ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጉደር ከተማ የወሰዷት፣ ወ/ሮ ትዕግስት በፀበል ከህመምሽ ትፈውስሻለች በሚል እንደሆነ የተናገረችው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ከተጠመቀች በኋላ ከቲቢ ካንሰር ተፈውሰሻል ብለው ህዝብ ተሰብስቦ በቪዲዮ እንደተቀረፀች ለፖሊስ ገልፃለች፡፡

ከዚህም በኋላ ደግሞ ልጆቼንና ወርቄን ነጥቃኛለች የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ልጆችሽ የእኔ እንጂ የአንቺ አይደሉም መቧሏን ትናገራለች፡፡ “ አንድ ቀን የትንሿን ልጄን ፀጉር ሳበጥር ለምን ነካሻት ተብዬ እስከምዝለፈለፍ ድረስ ተደብድቤያለውሁ” ትላለች፡፡

ከእኔ የትም አታመልጡም ስለምትል ሁሉም ይፈራታል የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ተከታዮቿ “ እመቤታችን ናት አምልኳት” እንደሚሉ ትናገራለች፡፡ “በምስል ታመልካላችሁ፤ ይሄው በአካል መጥታለች አምልኳት” ይሉናል ብላለች፡፡ በየቀኑ ፆም አለ፣ በቀን አንዴ ንፍሮ እንበላለን ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ፆሙ የአዋቂ ብቻ ሳይሆን ከስድስት ወር ጀምሮ ያለ ህፃንም እንዲፆም ይደረጋል- ለሦስት ቀን ጡት አይሰጠውም ብላለች፡፡

ወ/ሮ ትዕግስት ትምህርት ሃጢያት ነው በሚል አቋም ልጆች እንዳይማሩ እንደምታደርግም ተበዳይዋ ለፖሊስ ተናግራለች፡፡ የ12 ዓመት ልጄን ከዚህ እንግልት ለማዳን እንጥፋ ብዬው ነበር ፣ እሱ ግን ፈርቶ እምቢ አለኝ የምትለው- አለሚቱ፣ የባሰው መከራ የመጣው ግን የ3 አመት ልጄ ለ3 ቀን ያለ እህል ውሃ ፆም ፀሎት መያዝ አለበት ስትላት እንደሆነ ተናግራለች፡፡ ትልቁ ልጄ አሻፈረኝ ስላለ ሌላ ሙከራ ባደርግ ይገሉኛል ብዬ ትንሿን ልጄን ይዤ ጠፋሁ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ የወንድ ልጇ ነገር ስላላስቻላት ተመልሳ ወደ አምቦ መሄዷን ትናገራለች፡፡

ሆኖም ሰው ሁሉ ስለጠላቸው ወደ አዲስ አበባ ሄደዋል ተብላ መመለሷንና ልጇን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማግኘቷን ገልፃ ለሳምንት ያህል አብሯት ከቆየ በኋላ እንደጠፋ ገልጻለች፡፡ ፖሊስ ልጇን ለሁለተኛ ጊዜ አግኝቶ የሰጣት ቢሆንም ተስማምተው ሊኖሩ እንዳልቻሉ እናት ትናገራለች፡፡ እኔን እንደ እናቱ ሳይሆን እንደ ጠላት ነው የሚያየኝ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ “ ማርያምን ከሰሻት እኔ ካንቺ ጋር አልኖርም” ይላት እንደነበር ገልፃለች፡፡ ልጄ “ እኛ ምድራዊ አይደለንም፣ ሰማያዊ ነን” እያለ እሷ የምትናገረውን ሲደግም ነገሩ ከአቅሜ በላይ እንደሆነ ስለገባኝ ወደ እነሱ እንዳይመለስ በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ተደርጓል የምትለው እናቱ አሁን ትንሽ ቢሻሻልም፣ እሷን ግን እንደጠላት እንደሚመለከታት ትናገራለች፡፡ ልጄ ጤነኛ አይደለም ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፣ ንብረቴን በሙሉ አጥቼአለሁ ከምንም በላይ የሚፀፅተኝ ግን ልጄን ማጣቴ ነው ብላለች- እንባዋን እያፈሰሰች፡፡

ወ/ሮ ትዕግስት አበራ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ ስትሆን ጉዳይዋ ወደ ፍርድ ቤት ተልኮ በጊዜ ቀጠሮ ላይ ነው፡፡ ወ/ሮ ትዕግስት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል “ የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ እኔ ከወንድ ጋር አልተኛሁም፤ ተርፌሳም፣ ማርያምን ዮሴፍ ይጠብቃት እንደነበር ጠባቂዬ ነው፡፡ ሦስት ልጆች ቢኖሩኝም በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው፣ ይህንን ሁሉ ያደረኩት ሥላሴዎች አዘውኝ ነው፣ አላጠፋሁም” ብላለች፡፡

ምንጭ (ሳምንታዊው አዲስ አድማስ ጋዜጣ -ሰላም ገረመው)

20110429

ከሦስት ሺሕ በላይ ኢአማንያን ዳግመኛ ተወለዱ።

ከሦስት ሺሕ በላይ ኢአማንያን ዳግመኛ ተወለዱ።

በከንባታ ጠንባሮ እና አላባ ሀገረ ስብከት በተካሔደ ሐዋርያዊ ጉዞ ከሦስት ሺሕ ስድስት መቶ በላይ ኢ አማንያን ተጠምቀው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጅነትን አግኝተዋል።

የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ለስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በላከው ደብዳቤ እንዳስታወቀው፤ የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር በሸፈነው ሙሉ ወጪ የካቲት 19 ቀን 2003 ዓ.ም በተደረገው ሐዋርያዊ ጉዞ በርካታ ምእመናን ቃለ እግዚአብሔርን ከማግኘታቸው በተጨማሪ የሌላ እምነት ተከታዮችም በመጠመቃቸው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል።

ጉባኤው በተ ደረገባቸው በዱርጊ መንበረ ሰብሐት ቅድስት ማርያምና በእምብኩና ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሺሕ ሦስት መቶ ሠላሳ አንድ፤ በሀደሮና ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ በኦጆራ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ አንድ ሺሕ ሦስት መቶ ስልሣ አራት በአጠ ቃላይ ሦስት ሺሕ ስድስት መቶ ዘጠና አምስት የሌላ እምነት ተከታይ የነበሩ በብፁዕ አቡነ ቀለምኒጦስ የከንባታ ሀድያ ስልጢ ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ እጅ ተጠምቀዋል፡፡
ብፁዕነታቸው በዚሁ ወቅት እንደተ ናገሩት፤ የሥላሴን ልጅነት ያገኙትና በፍቅሩ ወደ ቅድስና ስፍራው የመጡት ሁሉ ሦስት መንፈሳዊ ጸጋዎችን ማለትም፤ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግመኛ መወለድን፣ በቅብዓ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ /ዘይት/ መክበርን፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበልን አግኝተዋል፡፡

«የእግዚአብሔር ዓላማ ማንም ሰው የመንግሥቱ ወራሽ እንዲሆን ነው፡፡ ዛሬ የተጠመቃችሁትም የእግዚአ ብሔር ልጆች ሆናችኋል» ያሉት ብፁዕነታቸው፣ «የእግዚአብሔር መንግሥትን ለመውረስ የሚያስችላችሁን መልካም ሥራ መሥራት፣ በጸሎትም መትጋት እና በሃይማኖት መጽናት ያስፈልጋል፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች ስለሆናችሁ ከማኅበረ መላእክት እና ከቅዱሳኑ ስለተቀላቀላችሁ ደስ ይበላችሁ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሥጋዊውም ሆነ መንፈሳዊ ሕይወታችሁ ትጸልያለች» ብለዋል፡፡

የከንባታ ጠንባሮ አላባ ሃገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ አባ ሚካኤል ገብረ ማርያም በበኩ ላቸው፤ ጥምቀቱን ተቀብለው የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ልጅነትን ያገኙት ምእመናን፣ በክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መጠንከር፣ በጸሎት መትጋትና መማር እንዳለባቸው አሳስበው ወደፊ ትም፤ «እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነታቸው ባላቸው ሙያ ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማገልገል እና በእርሷም የመገልገል መብት አላቸው» ብለዋል፡፡

«በዛሬው ዕለት የተጠመቃችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ከጨለማ ወደ ብርሃን ዘለዓለማዊ ሕይወት ተሸጋግራችኋል፡፡ ስለዚህ መንግሥተ እግዚአብሔርን የሚያስገኝ በጎ ሥራ እንድትሠሩ በጾም በጸሎት ትጉ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለእናንተ የሚገባችሁን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነች» ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ ሀገረ ስብከቱ ሕዝቡን በትጋት ለማገልገል ቃል መግባቱን ተናግረዋል፡፡

/ ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ሚያዝያ 1-15 2003 ዓ.ም /

20110215

ወለንኪ ቅዱስ ዮሓንስ ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በቃጠሎ ሙሉ ለሙሉ ስለመዉደሙ



ባለፈው አመት ጥር 2002 ዓ.ም ከ አስገራሚው እና ታሪክን በ ሰሩ ወጣቶች ተከብሮ ከዋለው የ ጥምቀት በዓል በኃላ የተሰማው አስደንጋጭና አሳዛኝ ዜና ነበር:: እሱም በምዕራብ ሽዋ ከ አዲስ አበባ 65 ኬ.ሜ እርቆ የሚገኘው የ ወለንኪ ቅዱስ ዮሓንስ ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ባልታወቁ ወገኖች ሙሉ ለሙሉ መቃጠል ነበር:: በቃጠሎው ከታቦቱ በስተቀር መላው ቤተ ክርስቲያኑና ንዋየ ቅዱሳት ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል::ይህም ድርጊት በከተማዋና በዙሪያዋ ብሎም በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የተዋህዶ ልጆች እና ሀገራቸዉን የሚወዱ ወገኖችን ያስቆጣ ነበር እኩይ ተግባር ነበር:: በአጭር ጊዜ ዉስጥ ቤተክርስቲያኑ ተሰርቶ ንዋያተ ቅዱሳት ተማልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምራል::አሁን ግን ያ ሁሉ አልፎ ቤተክርስቲያንዋ እንደገና አገልግሎት መስጠት ጀምራለች ሁሉን ያከናወነልን እግዚአብሔር ይመስገን:: "የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።" ማቴ 16:18 ግራኝ አህመድም ዮዲት ጉዲት ሁሉም ተዋህዶን ለማጥፋት ሞከሩ አልቻልሙም ይልቁንስ እየሞትን በዛን በመግደል ጽድቅ እንደሌለ በ እርግጥ አሳይተናል ለምሳሌ ፓዉሎስ አንገቱን ተሰየፈ ጴጥሮስም ተሰቀለ ብዙ ቅዱሳን በ ስቃይ እንዳለፉም እናዉቃለን የተዋህዶ ልጆች ዛሬም በ ስቃይ በፈተና ማለፍን ከ አባቶቻችን ተምረናል እና ቀዳሚ በሆነችው ተዋህዶ እንጽና ፍቅርን ያስተማረን የ እግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው እና ክፉን አትፍሩ

20110201

ጻድቁ አባታቺን አቡነ ተክለ ሃይማኖት



አቡነ ተክለኃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኃረያ መጋቢት መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታሕሣሥ ፳፬ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው «አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለው ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ወይም ደስታዋ ማለት ነው፡፡

ወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በአሥራ አምስት ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ኃሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም የኃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡
አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ

«አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ . . . ደካማ ለሆንኩ ለእኔ ያለ አንተ የሚያፀናኝ የለም። ለምፍገመገም ለእኔ ያለ አንተ ደጋፊ የለኝም። ለወደቅሁ ለእኔ ያለአንተ የሚያነሳኝ የለም። ለአዘንኩ ለእኔ ያለአንተ የሚያረጋጋኝ የለም። ለድሀው ለእኔ ያለ አንተ መጠጊያ የለኝም፡፡»

/ገድለ ተክለ ኃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫

ይህን ብለው ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ኃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን ክታቡ ስለ ቅዱሳን መንፈሳዊ ተጋድሎ ሲገልፅ:-

* «እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሱ» /ዕብ. ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ / እንዳለ አባታችን ቅዱስ ተክለሃይማኖትም በመንፈሳዊ ተጋድሎ እንዲሁም በትህትና በተአምራት አላዊ የነበረውን ንጉሥ ሞቶሎሚን ወደ ክርስትና መልሰዋል፡፡
* «ጽድቅን አደረጉ» እንዳለው አባታችን ወንጌልን በተጋድሎ ሕይወታቸው ተርጉመዋል፡፡
* «የአንበሶችን አፍ ዘጉ» ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ /ምዕ ፲፩ ቁ ፴፬ /እንዳለው አባታችንም የአውሬውን ፥ የዘንዶውን ራስ ቀጥቅጠዋል።
* «ከሰይፍ ስለት አመለጡ» እንዳለው አባታችንም ሞቶሎሚ ከወረወረው ጦር በተአምራት ድነዋል፡፡
* «ከድካማቸው በረቱ» እንዳለው አባታችንም ያለ ዕረፍት በብዙ ተጋድሎ በጾምና በስግደት በብዙ መከራ በርትተዋል፡፡

ይህን ሁሉ ገድልና ትሩፋት እየፈጸሙ ዕረፍታቸውም በደረሰ ጊዜ ደቀመዝሙሮቻቸውን «ልጆቼ ሆይ ሁሉም መነኮስ መንግሥተ ሰማይ ይገባል ማለት አይደለም፤ ዓለምን በሚገባ የናቀ ብቻ ይገባል እንጂ መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ጽድቁን ብቻ ፈልጉ፤ ጾምና ጸሎትን አዘውትሩ፤ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ ትእዛዛቱንም አጥብቃችሁ ጠብቁ እያሉ ይመክሯቸው ነበር. . .» በኋላም «ለዓለም ጨው ለራሴ አልጫ ሆንኩ፤ ለዓለም ብርሃን ለራሴ ጨለማ ሆንኩ፣ ከእውነተኛው ዳኛ ከጌታዬ ፊት ስቆም ምን እመልሳለሁ?» እያሉ በፍጹም ትህትና እና በልዩ መንፈሳዊ ተመስጦ ይጸልዩ ነበር፡፡

በመጨረሻም አባታችን በነሐሴ ፳፬ ቀን ዕረፍታቸው ሆነ፡፡ በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችንለእኚህ ዕረፍታቸው በእግዚአብሔር ፊት ለከበረና ብዙ ክብር ለተሰጣቸው ለጻድቁ ተክለሃይማኖት በየዓመቱ በነሐሴ ፳፬ቀን በዓለ ዕረፍታቸውን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ እኛንም ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡



ስብሐት ለእግዚአብሔር

20110115

1. ምስጢረ ሥላሴ


ሥላሴ ማለት የግእዝ አጠራር ነው። ትርጉሙ ሦስትነት ወይም ሥሉስነት ማለት ነው። የምስጢረ ሥላሴ ሁኔታ በዘመነ ብሉይ እንደ አሁኑ /ዘመነ ሐዲስ/ ግልጽ አልነበረም። ይህ ለብዙ ዘመናት ለጥቂቶች ግልጽ ለብዙዎች ግን ሥውር ሆኖ የነበረው ምስጢር ጐልቶ የወጣው በክርስቶስ መገለጥ ወይም ሥጋችንን ለብሶ ወደዚህ ዓለም መምጣት ነው። ጌታ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ ምስጢረ ሥላሴ በማያሻማ መልኩ ተገልጧል /ማቴ 3፥16/::

ሥላሴ ስንት ናቸው? ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ ሥላሴ አንድም ሦስትም ይሆናሉ /ናቸው/ የሚል ነው። ይህን መልስ ተከትሎ የሚመጣ ጥያቄም አለ እሱም ''ሥላሴ በምን አንድ ይሆናሉ በምን ሦስት ይሆናሉ'' የሚል ነው። የሁሉም መልስ ቀጥሎ ያለው ነው።

የሥላሴ አንድነት

ስለ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ስናነሳ ቀድመን የምንመለከተው ''አንድነትን'' ነው። ይህም የሆነበት ምክንያት ለአንድነታቸውና ለሦስትነታቸው መቀዳደም ኑሮበት ሳይሆን የቁጥር መሠረት አንድ ስለሆነ በዝያው ለመጀመር ነው /እንዘ አሐዱ ሠለስቱ ወእንዘ ሠለስቱ አሐዱ/ ሥላሴ አንድ ይሆናሉ በምን? በዐይነ ሥጋ የማይታይ የሰው አዕምሮ የማይመረምረው፣ የሰው ሕሊና አስሶ የማይደርስበት ከዓለም በፊት የነበረ በማዕከለ ዓለም ያለ፣ ዓለምን ኣሳልፎ የሚኖር አምላክ መኖሩን እናምናለን። እርሱም ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር ነው።

በምን አንድ ይሆናል ለሚለውም፦

1. በመለኮት:- መለኮት ማለት "መለከ - ገዛ" ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሆኖ ''ግዛት'' ማለት ነው። በእብራይስጥም ማልኮት ይባላል። እንግዲህ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በመለኮት ይህም ማለት በግዛት በመንግስት አንድ ናቸው። ለዚህም ቅ/መጽሐፍና አበው ተባብረውበታል።

- ''መንግስትህ የዘለዓለም መንግስት ናት ግዛትህም ለልጅ ልጅ ነው::" /መዝ 144፥13/ /መዝ 145፥10/ /መዝ 73፥12/
/ዳን 4፦3/ /ዳን 4፥34/ /1ተስሎ 2፥12/
- "በእርሱ የመለኮት ሙላት ሁሉ በሰውነት ተገልጦ ይኖራልና::" /ቈላስ 2፥9/
- የመለኮቱ ኃይል በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰለ ---ሁሉን ስጠን /2ጴጥ1፥3/
እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን ''መለኮቱ'' አለ እንጂ ''መለኮቶች'' በማለት አላበዛውም።

አበው ይህን መነሻ በማድረግ ያሉትንም እናስከትላለን::

+ ዮሐንስ ዘእስክንድርያ ''እስመ ምስጢረ ሥላሴ ይትሌለይ በአካላት ወኢይትሌለይ በመለኮት። ወመለኮቶሙስ አሐዱ ውእቱ። አኮ ከመ ዘርሁቃን ይትቃረቡ በበይናቲሆሙ በሱታፌ ተራክቦ አላ እሁዛን በጽምረተ አሐዱ መለኮት" ብሏል።

+ ሚናስ ዘእስክንድርያ:- "መለኮትኒ ይትዐወቅ ከመውእቱ ያኅብር ቅድስተ ሥላሴ።"

+ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ:- "መጻሕፍትሒ ቅዱሳት ያቤይና ከመውእቱ አሐዱ መለኮት'' ካለ በኋላ "ወበዝንቱ አዕመርነ ከመ አሐዱ ውእቱ መለኮት ዘቦቱ ሠለስቱ አካላት'' ብሏል።

+ ዲዮናስዮስ ዘእስክንድርያ:- "ይሤለሱ በአካላት ወይትዋሐዱ በመለኮት ወሶበሂ ንሬሲ ቅድስተ ሥላሴ ፍሉጣነ መለኮት ዘከመ አካላቲሆሙ ንትአመን እምነተ ሰይጣናዌ::'' ብሏል:: ሊቁ በተጨማሪም ''ንህነሰ ከመዝ ንሰግድ ለአሐዱ አምላክ ባሕቲቱ ወንትአመን በአሐዱ መለኮት ዘሠለስቱ አካላት ወኢንበውእ ኅበ ከፊለ መለኮት ወመንግስት'' ሲል አስተምሯል።

እነዚህ ደጋግ አባቶች እግዚአብሔር በመለኮት አንድ መሆኑ በማያሻማ መንገዱ አመስጥረው አስቀምጠውታል።

ርዕሱን ከማጠቃለላችን በፊት ከቤተክርስቲያን አባቶች ውጭ የሆነ ዋርፊልድ የተባለ ፀሓፊ ያለውን እንጥቀስ።

ዋርፊልድ ስለ ቅድስት ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት የሚከተለውን ጽፏል:: ''መቼም ቢሆን ቃላት ነገረ-እግዚአብሔርን በትክክል ሊገልጹልን አይችሉም። ቢሆንም ግን አንድን ነገር ለማብራራት ሌላ አማራጭ ስለሌለን የትም አንሄድም ''አንድና እውነተኛ አምላክ አለ። ይህም አንድ አምላክ ሦስት እኲል አካላት በመለኮት አንድ የሁኑ በአካል ግን የተለዩ አሉት'' ብሏል። /ዋርፊልድ የቲኦሎጂ ትምህርት ቢኖረውም ዓለማዊ ፀሓፊ ነው።/

ቤተክርስቲያን ትምህርት የተካኑት አባቶቻችን ሃይማኖታቸውን ይህን ይመስላል።

2. በባሕርይ:- ባሕርይ ማለት "ብሕረ ተንጣለለ፥ ሰፋ፥ ዘረጋ" ከሚለው ግስ የወጣ ነው። በቲኦሎጂ /በነገረ መለኮት/ ቋንቋ ሲፈታም ባሕርይ ማለት ሥርው፥ ነቅዕ አዋሃጅ /የሚያዋሕድ/ አስተገባኢ ማለት ነው። ባሕርይ አካል ሥራውን የሚሠራበት መሣሪያ ነው። አባቶች 'አንዳርጌ ሰብሰቤ' እንደማለት ነው ሲሉ "አስተጋባኢ" ብለውታል። ባሕርይና አካል እንደ አጽቅና እንደ ሥር አንድ ናቸው አይለያዩም አንዱ ያለ አንዱ መኖር አይችልም።

+ ባሕርይ ሥር፥ ምንጭ፥ አዋሐጅ የተባው ለምንድን ነው? ቢባል ሥርና ምንጭ ከእርሱ ለሚበቅለውና ለሚመነጨው ወይም ለሚወጣው ነገር ጥንትና መሠረት እንደሆነ ሁሉ ባሕርይም የአካልና የግብር የስምም መሠረት ነውና ሦስቱን አካላት የሚያስገኝና የሚያዋሕድ ስለሆነ ነው። እዚህ ላይ ባሕርይ መሠረት አስገኝ ስለተባለ ባሕርይ ከአካል ከስምና ከግብር ባነጋገር እንጂ በመኖር የሚቀድም ሆኖ አይደለም። ባነጋገር ግን የቁጥር መሠረት አንድ ስለሆነ ነገርን ከስሩ ለማምጣት 3 ከሚሰኙበት ነገር አንድ የሚሰኙበት ነገር መነሻ ማድረግ ስለሚገባ ነው። በዚህ መሠረት ሥላሴ በባሕርይ አንድ የሚሆኑበት ሥረ-ነገር ምንድን ነው? ያልን እንደሆነ:-

- መፍጠር:- ''አቤቱ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ ሰማያትም የእጅህ ሥራ ናቸው:: /መዝ 101፥25/ አሁን የተመለከትነው ጥቅስ ''ምድርን መሠረትህ'' ሰማያትም የእጅህ ሥራ ናቸው አለ እንጂ::

- ምድርን መሠረታችሁ የእጃችሁ ሥራ አላለም።

- ከዚህ በተጨማሪ ሥላሴ በመፍጠር ባሕርያቸው አንድ እንደሆኑ ብዙ መጥቀስ ቢቻልም ጥቂቱን ብቻ እነሆ (ዘፍ 1፥1) (ኢሳ 44፥24) (ኢሳ 40፥22) (ኢሳ 66፥2) (ኤር 10፥12) (ኤር 51፥15)

- ከዚህ በተጨማሪ ሥላሴ በባሕርይ አንድ የሚሆኑባቸው ነገሮች

መስጠት፣ መንሳት፣ መግደል፣ ማዳን ባጠቃላይ ሁሉም ቻይነት፥ ግዛት ጥበብ፥ ዕውቀት ምክር፥ ሥምረት እንዲህ ያለ ስመኛ ቃል ሁሉ የባሕርይ አንድነታቸውን ያሳያል። ይህም በመሆኑ ቅድምናቸውና ዕሪናቸው አንድ ነው። መቅደም መቀዳደም፣ መብለጥ መበላለጥ የለባቸውም። ይህ ሁሉ የሆነው ባሕርያቸው አንድ በመሆኑ ነው፦

ቅ/ቄርሎስ ''ኢይቀድም አሐዱ እምካልዑ : ወካልኡ እምሣልሱ አሐቲ ቅድምናሆሙ ለሥላሴ። ኢሀሎ አብ ዘመነ ዘእንበለ ወልዱ ወመንፈሱ አሐተ ስዓተ-ወኢ ከመ-ቅጽ በተዓይን። ሥላሴ ዕሪት ዘእንበለ ፍልጠት::

3. በኅልውና:- ሕልውና ማለት "ነዋሪነት፥ ኑሮ፥ አነዋወር" ማለት ነው። በነገረ መለኮት ቋንቋ አፈታት ግን አብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ኅልው ሆኖ፣ ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ኅልው ሆኖ፣ መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ኀልው ሆኖ በመኖር አንድ ናቸው ማለት ነው። በሌላ አባባልም ህልውና ሦስትነታቸውን ሳይጠቀልለው፣ ሦስትነትም አንድነታቸውን ህልውናውን ሳይከፍለው አንዱ ከአንዱ ጋራ ተገናዝቦ ባንድነት መኖር ነው። /በኲነት ርዕሳችን የበለጠ ይብራራል/

- ጌታ ስለ ኅልውናቸው አንድነት የሚከተለውን ብሏል። ''ኢተአምንሁ ከመ አነ በአብ ወአብ ብየ'' /ዮሐ 14፥9-11/

+ ዮሐንስ ዘእስክንድርያ:- "ነአምን እስመ አብ ህልው በወልድ ወበመንፈስ ቅዱስ። ወወልድኒ ኅልው በአብ ወበመንፈስ ቅዱስ፣ ወመንፈስ ቅዱስኒ ህልው በአብ ወበወልድ።" እንዳለ/ የሥላሴ አንድነት እኛ ከምናውቀው ''አንድ'' የተለየ ነው በዚህ አንድነት ውስጥ ሦስትነት አለና ይኸውም የሚከተለው ነው::
. ይቀጥላል