20101016

በ እኛ ነዋየተ ቅዱሳን የመናፍቃን ጭፈራ

የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።

የማቴዎስ ወንጌል7፥15

ዛሬ ይህን ለመጻፍ ያስገደደኝ ትላንት አንድ ጋደኛዬ ኢትዮ ትዩብ በሚለው ድህረ ገጽ ላይ የወጣዉን ምስለ ድምጽ ( http://www.ethiotube.net/video/8669/Yetsidiq-Tsehay-Ethiopian-Gospel-Singers%EF%BB%BF ) መናፍቅኑ ከዚህ በፊት በ ቅድስት ቤተክርስትያናችን ላይ ያልሆኑ ስብከቶችን እና የ እኛ የ ሆኑ የዘማ እቃዎችን በመጠቀም ሲዘፍኑ አይተናል በዚም አላበቁም ከ 4 እና 5 አመታት በፊት ዉዳሴማሪያምን ቀየር አድርገዉ ዘመን ባፈራዉ የድምጽ መሳሪያ በመጠቀምን ሲዘፍኑም አይተን አልፈናል የቅርብ ጊዘዉን ላስታዉሳቹ አንድ በልመና የሚተዳደር ሰዉን በገንዘብ ይሁን በሃይ በማስፈራራት አቡነ ያሬድ ነኝ ብሎ የሃሰትምስክርነት እንዲሰጥ ተደገ ይህንንም በዝምታ አለፍን.ለ ኢትዮጲያ ድህነት ተጠያቂዎ የ ኦርቶዶክስ በተክርስትያን ናት ሲሉም አድምጠን አልፈናል

እዚህ ላይ ሳልጠቅስ ማለፍ የማልፈልገዉ ነገር የ መምህር ዘበነን እዉነትን የማዉጣት ስራ ሊበረታታ ይገባዋል . የ ሃይማኖት መሪዎቻችንም በዚህ ነገር ላይ መላ ቢሉ ጥሩ ነው እላለው

ይሄን ቪድዮ ከሌላዉ ለየት የሚያደርገዉ የከበሮዉ፣ የፀናጽሉ፤ የመቋሚያው አላንስ ብሎ መፆረ መስቀሉን፣ጽናውን፣ ቃጭሉን ይዘዉ ሲጨፍሩ አየን ይህንንስ በዝምታ ማለፍ ያለብን አይመስ ለኝም. አባቶቻችን ያቆይልንን የዜማ መሳሪያዎችን እና ንዋያተ ቅዱሳቱን ይዘው ሲጨፍሩ ዝም ካልን የሚቀትለዉ ታቦትን ይዘዉ ይሆናል የሚጨፍሩት.

የቀደሙት አባትኦቻችን ያቆዩልንን ኦርቶዶስ ተዋህዶን እኛም ከ የዜማ መሳሪያዎቻቻን እና ንዋያተ ቅድሳቱ ከሙሉ ሚስጥርና ትርጉማቸው ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፉ የእኛ ሀላፊነት ነው።

ተኩላዉ ለምድ ለብሶ በርግጥ መጣል እና

አምላክ ሆይ አድነን ፍጠን ተሎ ና

20101006

እንኳን ለዘመነ ጽጌ በስላም አደረስን

ጌታ ሲወለድ ሰብአ ሰገል «የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት አለ? በምሥራቅ ኮከቡን አይተን ልንስግድለት መጥተናል» እያሉ በኮከብ እየተመሩ በመጡ ጊዜ በይሁዳ በገሊላና በሰማርያ የሮማውያን ተወካይ የነበረው ንጉሥ ሄሮድስ የጌታችን ንግሥና ምድራዊ ንግሥና መስሎት መንግስቴን ሊቀማኝ ነው ብሎ ደነገጠ፡፡ ፊሪሳውያን «መሲህ ተወልዶ ከሮማውያን አገዛዝ ነጻ ያወጣናል፡፡» ብለው ያምኑ እንደነበር ስለሚያውቅም ይህ የተፈጸመ መስሎት ጭንቀቱ በረታ፡፡ የተወለደውን ሕፃንም ለመግደል ተነሳ፡፡
ስለዚህም ሰብአ ሰገልን አስጠርቶ «ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ፤ ባገኛችሁትም ጊዜ እኔም እንድሰግድለት ወደ
እኔ ተመልሳችሁ ያለበትን ንገሩኝ» በማለት በሽንገላ ተናገራቸው፡፡
ጠቢባኑም ከሄሮድስ ከተለዩ በኋላ በኮከቡ እየተመሩ ጉዞአቸውን ቀጥለው ጌታችንን ከእናቱ ጋር አገኙት ፤ ተንበርክከው ሰገዱለት፤ ወርቅ ፣ ዕጣን፣ ከርቤ እጅ መንሻ አቀረቡለት፡፡
የእግዚአብሔር መልአክ ወደ ሄሮድስ እንዳይመለሱ ነገር ግን መንገድ ቀይረው ወደ ሀገራቸው እንዲሄዱ በነገራቸው መሠረት በሌላ መንገድ ወደ መጡበት ተደብቀው ተመለሱ፡፡
«እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ «ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነስ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሸ እስክነግርህም በዚያ ተቀመጥ አለው፡፡ » /ማቴ. 2 13 14/.......ዮሴፍም ተነሣ በዕድሜዋ በጣም ልጅ የነበረችው እመቤታችን ገና የተወለደውን ሕፃን አቅፋ የምትቀመጥበት አህያም ተዘጋጀ፡፡
ጉዞአቸውን ጀመሩ........
በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6 ዘመነ ጽጌ ወርኃ ጽጌ ይባላል:: ይኸውም ተራሮችን ሸንተረሮችን በአበባ ያስጌጠ ሰማይን በከዋክብት ያጌጠ ምድርን በስነ ጽጌያት ያሸበረቀ አምላክ ነው እና:: እሱ የሚመሰገንበት ስለሆነ .....ሌላው ጽጌ የተባለች እናቱ ድንግል ማርያም ፍሬ የተባለ ልጇ እሱን ኢየሱስ ክርስቶስን አዝላ ከኢየሩሳሌም ምድረ እስራኤል ወደ ግብጽ እንዲሁም ወደ አገራችን ኢትዮጵያ የተሰደደችበትን በማሰብ ለአርባ ቀናት ያህል ምዕመናን በፈቃዳቸው ለበረከት ይፆማሉ:: ሊቃውንቱም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት እስከ ንጋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ድረስ «ጽጌ ጽጌ ዘሰሎሞን ወዳዊት ጽጌ አሮን ዘክህነት» እያሉ ያመሰግኗታል:: እመቤታችንም በስደቷ ወራት ብዙ መከራ ደርሶባታል ተርባለች ተጠምታለች ልጄን ይገሉብኛል ብላ ተጨንቃለች::
ጌታ ወደ ግብጽ የተሰደደው ለምንድን ነው ቢሉ?....
(አንደኛ)..ነቢዩ ኢሳያስ የተናገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው:: «ወይወርድ እግዚእነ ተጽእኖ ድበ ደመና ቀሊል» «ጌታችን በፈጣን ደመና ሆኖ ወደ ግብጽ ይወርዳል» ኢሳያስ 19 ቁ. 1
(ሁለተኛ).. በግብጽ አምልኮተ ጣኦት ብዝቶ ነበር እና አምልኮተ ጣኦትን ለማጥፋት ነው::
እመቤታችን ሶስት አመት ከስድስት ወር እስኪፈጸም ድረስ በብግጽ እናም በሀገራችን በኢትዮጵያ የስደት ጊዜ አሳልፋለች ማቴ..2 ቁ. 19
በስደት ከቆዩ በኋላ ሄሮድስ ሞተ።.....ሄሮድስም ከሞተ በኋላ እነሆ የጌታ መልአክ በግብጽ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ «የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል ሀገር ሂድ አለው፡፡ እርሱም ተነስቶ ሕጻኑንና እናቱን ይዞ ወደ እስራኤል ሀገር ገባ» ማቴ 2-19-21/
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከመስከረም 26 ቀን ጀምሮ እስከ ኅዳር 6
ቀን ድረስ የጌታን እና የእመቤታችንን ስደት በማሰብ የጽጌ ፆም ይፆማል
እንኳን አደረሳችሁ!!!

20101001

ስለ ጽዮን ዝም አልልም፥


ስለ ጽዮን ዝም አልልም፥ ስለ ኢየሩሳሌምም ጸጥ አልልም፥ ጽድቅዋ እንደ ጸዳል መዳንዋም እንደሚበራ ፋና እስኪወጣ ድረስ።አሕዛብም ጽድቅሽን ነገሥታትም ሁሉ ክብርሽን ያያሉ፤ የእግዚአብሔርም አፍ በሚጠራበት በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ።በእግዚአብሔር እጅ የክብር አክሊል፥ በአምላክሽም እጅ የመንግሥት ዘውድ ትሆኛለሽ።ምዕራፍ 62:1-3
መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና። ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች።መልአኩም እንዲህ አላት። ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።ሉቃ 1፤28-30 መልአኩ ገብርኤል እንዳመሰገናት እኛስ ብናመሰግናት ብንዘምርላት ክብራን ለ አለም ብንመሰክር ስተታቺን ምኑ ላይ ነው ?
ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች። አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው።የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ ዘሎአልና።ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት። የሉቃስ ወንጌል 1:41-45
ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።መዝሙረ ዳዊት 87:5
ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ ይፈሩ፥ ወደ ኋላቸውም ይመለሱ።መዝሙረ ዳዊት 129:5
የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻልትንቢተ ኢሳይያስ 60:14

20100513

why are you troubled about?


So I say to you, Take no thought for your life, about food or drink, or about clothing for your body. Is not life more than food, and the body more than its clothing?


See the birds of heaven; they do not put seeds in the earth, they do not get in grain, or put it in store-houses; and your Father in heaven gives them food. Are you not of much more value than they?


And which of you by taking thought is able to make himself a cubit taller?


And why are you troubled about clothing? See the flowers of the field, how they come up; they do no work, they make no thread:


But I say to you that even Solomon in all his glory was not clothed like one of these.


But if God gives such clothing to the grass of the field, which is here today and tomorrow is put into the oven, will he not much more give you clothing, O you of little faith?


Then do not be full of care, saying, What are we to have for food or drink? or, With what may we be clothed?


Because the Gentiles go in search of all these things: for your Father in heaven has knowledge that you have need of all these things:


But let your first care be for his kingdom and his righteousness; and all these other things will be given to you in addition.


Then have no care for tomorrow: tomorrow will take care of itself. Take the trouble of the day as it comes.
Matthew 6:25-34

አትጨነቁ

ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም፥ የሰማዩ አባታችሁም ይመግባቸዋል፤ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን? ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማን ነው? ስለ ልብስስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፤

አይደክሙም አይፈትሉምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም።እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፥ እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ እናንተንማ ይልቁን እንዴት? እንግዲህ። ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና።ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል። የማቴዎስ ወንጌል 6: 25-34

20100501

Jesus Calms the Storm



That day when evening came, he said to his disciples, “Let us go over to the other side.” Leaving the crowd behind, they took him along, just as he was, in the boat. There were also other boats with him. A furious squall came up, and the waves broke over the boat, so that it was nearly swamped. Jesus was in the stern, sleeping on a cushion. The disciples woke him and said to him, “Teacher, don’t you care if we drown?”He got up, rebuked the wind and said to the waves, “Quiet! Be still!” Then the wind died down and it was completely calm. He said to his disciples, “Why are you so afraid? Do you still have no faith?” They were terrified and asked each other, “Who is this? Even the wind and the waves obey him!”

Jésus calme la tempête


Et laissant les troupes, ils l'emmenèrent [avec eux], lui étant déjà dans la nacelle; et il y avait aussi d'autres petites nacelles avec lui.Et il se leva un si grand tourbillon de vent, que les vagues se jetaient dans la nacelle, de sorte qu'elle s’emplissait déjà. Or il était à la poupe, dormant sur un oreiller; et ils le réveillèrent, et lui dirent : Maître, ne te soucies-tu point que nous périssions? Mais lui étant réveillé, tança le vent, et dit à la mer : tais-toi, sois tranquille; et le vent cessa, et il se fit un grand calme. Puis il leur dit : pourquoi êtes-vous ainsi craintifs? comment n'avez-vous point de foi? Et ils furent saisis d'une grande crainte, et ils se disaient l'un à l'autre : mais qui est celui-ci, que le vent même et la mer lui obéissent?
marc 4:36-41