20140225

“ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው”


ዑጋንዳ የጸረ ግብረሰዶማውያን ሕግ አጸደቀች!

የዑጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ “አከራካሪ” ሲባል የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በፊርማቸው አጸደቁ፡፡ ግብረሰዶማውያንን “ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ” እና “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ ግብረሰዶማዊነት በምዕራቡ ዓለም አማካኝነት ወደ አፍሪካ እየተስፋፋ የመጣ ነው ብለዋል፡፡

ለበርካታ ዓመታት አከራካሪ ሆኖ የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊነት ሕግ ትላንት ዑጋንዳ አጽድቃለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም እና ሰዶማዊነት የመብት ጉዳይ እንደሆነ ከሚከራከሩ ተቋማት የደረሰባትን ውትወታ ወደ ጎን በማለት ዑጋንዳ በሕግ ማጽደቋ የበርካታ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሽፋን የሰጡበት ርዕስ ሆኗል፡፡ የሕጉን መጽደቅ አስመልክቶ ጥቂት ዑጋንዳውያን ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሲሆን በርካታዎች ደግሞ ድጋፋቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡
ሕጉን በፊርማቸው ያጸደቁት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ሲኤንኤን ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ግብረሰዶማውያን “አጸያፊ ሰዎች ናቸው፤ ምን ዓይነት ድርጊት ይፈጽሙ እንደሆነ አላውቅም ነበር፤ በቅርቡ የሰማሁት ግን በጣም አስደንጋጭ ነው፤ ጸያፍ ነው” ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ሲቀጥሉም ሰዶማውያን ሲወለዱ ጀምሮ እንደዚሁ ናቸው ስለተባለ ሁኔታውን እውነት አድርገው በመውሰድ ቸል ሊሉት እንደነበር ሆኖም ግን እስካሁን ምንም ሳይንሳዊ ማስረጃ እንዳልቀረበበት ተናግረዋል፡፡
ሙሴቪኒ ሕጉን እንዲያጸድቁ ያደረጋቸውን አንዱን ምክንያት ሲጠቅሱም፤ ግብረሰዶማዊነት ከጄኔቲክስ ጋር በተያያዘ ከውልደት ጀምሮ የሚመጣ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው በማለት ይገምቱ እንደነበር ሆኖም የአገራቸው ሳይንቲስቶች ይህንን መከራከሪያ ውድቅ ማድረጋቸውን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ሕጉ በፕሬዚዳንቱ ፊርማ ከጸደቀ በኋላ ወዲያውኑ በሥራ ላይ የዋለ ሲሆን ግብረሰዶማዊ ወሲብ ሲፈጽም የተገኘ ማንኛውም ሰው እስከ ዕድሜ ይፍታህ በሚደርስ እስራት እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ በወንጀሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ በ14ዓመት እስር ይቀጣል፡፡ በተደጋጋሚ ወንጀሉን ሲፈጽሙ የተገኙ፣ ዕድሜያቸው ካልደረሱ ጋር እንዲሁም ከአካለ ስንኩል ወይም ከኤችአይቪ ተጠቂ ጋር ወንጀሉን የፈጸሙ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ሕጉ ያዛል፡፡

ናይጄሪያም ከአንድ ወር በፊት ተመሳሳይ ሕግ ያወጣች ሲሆን የዑጋንዳው ሕግ በረቂቅነት ከወጣ የዛሬ አራት ዓመት ጀምሮ ምዕራባውያን ከፍተኛ ተጽዕኖ በማድረግ ሕጉ ተግባራዊ እንዳይሆን፤ ከሆነም በአብዛኛው የህጉ ክፍል እንዲሸራረፍ በርካታ ሙከራዎችን፣ ማስፈራሪያዎችንና ውስወሳዎችን ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡

በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኦባማ አፈቀላጤ የህጉን መጽደቅ “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ዑጋንዳ ባስቸኳይ ሕጉን እንድትሰርዝ የጠየቁ ሲሆን አሜሪካ ከዑጋንዳ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደገና እንደምታጤነውም ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንም በበኩላቸው የሕጉን መጽደቅ የኮነኑ ሲሆን የተወሰኑ የአውሮጳ አገራት ለዑጋንዳ የሚሰጡትን ዕርዳታ እንደሚያቋርጡ ዝተዋል፡፡ ሌሎች አገራት ግን እንዲህ ዓይነቱ የዕርዳታ ማቋረጥ ውሳኔ ዑጋንዳውያንን የሚጎዳ በመሆኑ እርምጃው መወሰድ የለበትም ይላሉ፡፡

የዑጋንዳ ሕግ አውጪዎች ያረቀቁትን ሕግ በፈረሙበት ጊዜ ሙሴቪኒ እንዳሉት ምዕራባውያን በዑጋንዳ ጉዳይ በግልጽ ጣልቃ እየገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ “አፍሪካውያን በሌሎች ላይ የራሳችንን አመለካከት አንጭንም” ያሉት ሙሴቪኒ ምዕራባውያን እስካሁን ያደረጉት ጣልቃገብነት ትክክለኛ እንዳልነበረ እና ይህም ደግሞ “ማኅበራዊ ኢምፔሪያዝም” ነው ሲሉ ኮንነውታል፡፡ ግትርና ግዴለሽ ምዕራባዊ ድርጅቶች የራሳቸውን አጀንዳ ለማስፋፋት እየጣሩ መሆናቸውንና ለዚህም ሰዶማዊነት ተግባር የኡጋንዳን ህጻናት እየደለሉ ወደ ግብረሰዶማዊነት ወንጀል እንደሚያስገቧቸው ከሰዋል፡፡ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሰዶማውያን ደሃ ዑጋንዳውያንን ዒላማቸው በማድረግ በገንዘብ በመደለል ለግብረሰዶማዊነት እንደሚጋብዟቸውና ቀጥሎም ለግብረሰዶማዊ አዳሪነት እንደሚዳርጓቸው ሙሴቪኒ ተናግረዋል፡፡

የዑጋንዳን ውሳኔ አስመልክቶ የማኅበራዊ ጉዳይ ባለሙያ የሆኑ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት “ኢህአዴግም ከየምዕራቡ ለሚለቃቅመው ዕርዳታ ብሎ የአገርን ባህልና ማኅበራዊ እሴት ከሚያጠፋ ይልቅ ተመሳሳይ ተግባር ሊወስድ ይገባዋል፤ የተቃወመውን ሁሉ “አሸባሪ” በማለት በጸረ አሸባሪ ህግ ስቃዩን ከሚያሳይ የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በማውጣት ይህንን በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን ወረርሽኝ መላ ሊለው ይገባል” ብለዋል፡፡

ናይጄሪያም ከአንድ ወር በፊት ተመሳሳይ ሕግ ያወጣች ሲሆን የዑጋንዳው ሕግ በረቂቅነት ከወጣ የዛሬ አራት ዓመት ጀምሮ ምዕራባውያን ከፍተኛ ተጽዕኖ በማድረግ ሕጉ ተግባራዊ እንዳይሆን፤ ከሆነም በአብዛኛው የህጉ ክፍል እንዲሸራረፍ በርካታ ሙከራዎችን፣ ማስፈራሪያዎችንና ውስወሳዎችን ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡
በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኦባማ አፈቀላጤ የህጉን መጽደቅ “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ዑጋንዳ ባስቸኳይ ሕጉን እንድትሰርዝ የጠየቁ ሲሆን አሜሪካ ከዑጋንዳ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደገና እንደምታጤነውም ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንም በበኩላቸው የሕጉን መጽደቅ የኮነኑ ሲሆን የተወሰኑ የአውሮጳ አገራት ለዑጋንዳ የሚሰጡትን ዕርዳታ እንደሚያቋርጡ ዝተዋል፡፡ ሌሎች አገራት ግን እንዲህ ዓይነቱ የዕርዳታ ማቋረጥ ውሳኔ ዑጋንዳውያንን የሚጎዳ በመሆኑ እርምጃው መወሰድ የለበትም ይላሉ፡፡


የዑጋንዳ ሕግ አውጪዎች ያረቀቁትን ሕግ በፈረሙበት ጊዜ ሙሴቪኒ እንዳሉት ምዕራባውያን በዑጋንዳ ጉዳይ በግልጽ ጣልቃ እየገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ “አፍሪካውያን በሌሎች ላይ የራሳችንን አመለካከት አንጭንም” ያሉት ሙሴቪኒ ምዕራባውያን እስካሁን ያደረጉት ጣልቃገብነት ትክክለኛ እንዳልነበረ እና ይህም ደግሞ “ማኅበራዊ ኢምፔሪያዝም” ነው ሲሉ ኮንነውታል፡፡ ግትርና ግዴለሽ ምዕራባዊ ድርጅቶች የራሳቸውን አጀንዳ ለማስፋፋት እየጣሩ መሆናቸውንና ለዚህም ሰዶማዊነት ተግባር የኡጋንዳን ህጻናት እየደለሉ ወደ ግብረሰዶማዊነት ወንጀል እንደሚያስገቧቸው ከሰዋል፡፡ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሰዶማውያን ደሃ ዑጋንዳውያንን ዒላማቸው በማድረግ በገንዘብ በመደለል ለግብረሰዶማዊነት እንደሚጋብዟቸውና ቀጥሎም ለግብረሰዶማዊ አዳሪነት እንደሚዳርጓቸው ሙሴቪኒ ተናግረዋል፡፡
የዑጋንዳን ውሳኔ አስመልክቶ የማኅበራዊ ጉዳይ ባለሙያ የሆኑ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት “ኢህአዴግም ከየምዕራቡ ለሚለቃቅመው ዕርዳታ ብሎ የአገርን ባህልና ማኅበራዊ እሴት ከሚያጠፋ ይልቅ ተመሳሳይ ተግባር ሊወስድ ይገባዋል፤ የተቃወመውን ሁሉ “አሸባሪ” በማለት በጸረ አሸባሪ ህግ ስቃዩን ከሚያሳይ የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በማውጣት ይህንን በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን ወረርሽኝ መላ ሊለው ይገባል” ብለዋል፡፡


ምንጭ ጎልጉል ጋዜጣ

20121103

ዘማሪት አቦነሽ አድናው ከኪነጥበብ ጋደኞቿ የሽኝት ፕሮግራም ተደረገላት

በትላንትናው ዕለት በተደረገው የእራት ግብዣ ለዘማሪት አቦነሽ አድነው መሸኛ ብዛት ያላቸው አርቲስት ጓደኞቿ በተሰበሰቡበት ንግግር በማድረግ የዘፋኝነት ስራዋን ለቃ ወደ እግዚአብሔር  አመስጋኝነት ወደ ዘማሪነት የተሸጋገረችና ለመጨረሻ ጊዜ የዘፈኑን ዓለም የተወችና ያቆመች መሆኑን ለአርቲስት ጓደኞቿና በዕለቱ ለነበሩት የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ተናግራለች። አቦነሽ ስትናገር እኔ ለ24 ዓመት በሙዚቃው አለም አገልግያለሁ ሙዚቃን በጣም እወድ ነበር ሙዚቃ ለኔ ትልቅ ባለውለታዬ ነው አለምን አዙሮ አሣይቶኛል እኔም አድጌበታለሁ ሙዚቃ ለህይወቴ ብዙ አስተዋፅኦ አድርጎልኛል። ኑሬበታለሁ ቤተሰቦቼን ረድቼ ልጆቼን አሣድጌበታለሁ። ግን ዘማሪ መሆንን የተመኘሁትን ያህል ድምፃዊ መሆንን ተመኝቼው አላውቅም ከአምስት ዓመታት በፊት ጀምሮ ልቤ ሸፍቷል ሁል ጊዜ አስበው ነበር ዘማሪ መሆን እግዚአብሔርን ማገልገል የበለጠ ዋጋ ያለው መሆኑን አውቅ ነበር። እናም እግዚአብሔር ይመስገን ተሳካልኝ ሀሣቤ ሞላልኝ ይሄው ዛሬ በምወዳችሁ የጥበብ ጓደኖቼ መካከል ከአሁን በኋላ ዘማሪ ነኝ! ለወደፊትም መፅሀፍ ቅዱስ ቁጥር እየጠቀስኩ ብዙ ስለ እግዚአብሔር ልነግራችሁ እወዳለሁ ስትል ጓደኞቿን ተማጥና ከዘፈን ዓለም መሠናበቷን አብስራለች። በእለቱ የተሰበሰቡት ጓደኞቿም ለአቦነሽ(አቢቲ) ያላቸውን ክብር ገልፀው። በጭብጨባ የስራ መልቀቂያ ፈቃድ ሰጥተው በዘፈን አለም በነበረችበት ጊዜ አብረዋት ስላሣለፉት ስለ ፅባይዋ በጣም ንፁህ ደግ ቅንና ከበፊትም በዘፈን ዓለም ላይ እያለችም ከአፏ የሚወጡት ከአንደበቷ የሚፈልቁት ቃሎቿ የተቀደሱ ክፉ ነገር የማይወጣት የዘፈነችው የሚያምርባት ስትስቅ ስትጫወት ተወዳጅ የሆነች ትሁት በመሆኗ የመረጠችው መንገድ የሚገባትና ጥሩ የእግዚአብሔር አገልጋይ ልትሆን የምትችል መሆኗን በዕለቱ እየተነሡ ምስክርነት ሰጥተዋል። በምሽቱ የእራት ግብዣ ላይ አብረዋት ሲዘምሩ ሲያሸበሽቡ ብሎም በግጥም ስንኝ የቋጠሩላትም አንጋፋ አርቲስቶችም ነበሩ።
ተነሡ ለምስጋና(3)
ለዚህ ላበቃን እንዘምርለት
በዙፉኑ ፊት እንስገድለት!
እያለች አዲስ የሰራችውን መዝሙር በጣፋጭ ድምጿ ስትዘምር ከፊቷ ደስታና ብሩህ ህይወት ይታይባት ነበር።
በዕለቱ ከነበሩት ታላላቅ አርቲስቶች መካከል ታላቋ የኪነ-ጥበብ ሰው አርቲስት አለምፀሃይ ወዳጆ ስለ አቢቲ የሙዚቃ አነሣስና ታሪክ በጥቂቱ እንዲህ ስትል ተደምጣለች።
አቢቲ የተወለደችው በደቡብ ኢትዮጵያ በሃይቆችና ቡታጅራ አዉራጃ በሶዶ ወረዳ ቡኢ በምትባል ትንሽ ገጠር መንደር ሲሆን በጊዜው የነበሩት የሙዚቃ ጥበብ ባለሙያዎች ወደ አቢቲ መንደር ወደ ቡኢ በወረዱበት ጊዜ አቢቲን ለሙዚቃ አጯት። እሷም ሁል ጊዜ በዚህ በኪነጥበብ ሙያ ውስጥ ባለውለታዋ የሆኑትን ኮረኔል ለማ ደምሠውንና አርቲስት አየለ ማሞን ሁልጊዜ ታነሣለች። አቢቲ ገና ሙዚቃን የጀመረችው በድሮው የክቡር ዘበኛ የሙዚቃ ቡደን ውስጥ ነው ሀ ብላ ሙዚቃን የተቀላቀለችው። ከዚያ በኋላም ባሳተመችው “ባላገሩ” “ባህሌን” በተሰኙ ሲዲዎቿ  ተወዳጀነትን ያተረፈች ሲሆን አቢቲ መቼም በኢትዮጵያ የሙዚቃ ህይወት ሁላችን አርቲስቶችም ሆንን የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚያውቀው ሙዚቃን ደምቃበታለች፣ አለምን ዞራበታለች፣ ታጅባበታለች፣ ተምነሽንሻበታለች በትላልቅ መድረኮች ላይ የመስራት እድል አግኝታበታለች። በዚያም መጠን ደግሞ ተወቅሣበታለች፣ ተከሣበታለች፣ በሬዲዮ ተወግዛበታለች እናም በተለያዩ ሁኔታዎች በማለፍ የሙያ አስተዋፀኦ አበርክታበታለች። አቢቲ ገና ስትጀምር ጀምሮ ከታላላቅ አርቲስቶች ከነ ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ ከነ ብዙነሽ በቀለ እና ሌሎችም በነበሩበት የጀመረች በመሆኑ እስከ መጨረሻው በዚህ በአሜሪካም ከታላላቅ አርቲስቶችና ታላላቅ መድረኮችን የማግኘት እድልም አግኝታለች። በግሏ በአቢቲነቷ  በአለም አቀፍ መድረክ እንደነ ኬኔዲ ሴንተር ባሉ ቦታዎች በመገኘት ተጫውታ ሌሎችንም ተከታዮችና አድናቂዎችን ያገኘች አርቲስት ናት።
እግዚአብሔር ለዚህ ካበቃሽ እንግዲህ እኛም ያንቼን እድል ይስጠን እያልን ባለችበት ፀንታ፣እንድትቆይ እየፀለይን እየደገፍናት፤ እያገዝናት የሀሣቧ ተከፋይ እየሆንን እንዳንለያት። እኛንም እንደ እሷ እንዲያበቃን እንፀልያለን። አቢቲ ታመሽ በነበርሽበት ወቅት ድጋሜ ህይወት ከሠጠኽኝ ጌታዬ ለአንት አገልጋይህ እሆናለሁ ባልሽው መሠረት ባገኘሽው ድጋሜ ህይወት አምላክሽን ለማመስገን መልካሙን መንገድ መርጠሻልና ስምሽም ገና ከማለዳው የተሠጠው “የአቦ ነሽ” ነውና አቦዬ ብርታቱን ፅናቱን እንዲሰጡሽ በእኔና በጓደኞችሽ ስም እመኝልሻለሁ በማለት አርቲስት ዓለምፀሃይ ወዳጆ እና ሌሎችም ጓደኞቿ መልካሙን በመመኘት ስትዘምር እየዘመሩ፣ ስታሸበሽብ እያሸበሸቡ፣ ምሽቱን አብረዋት በመሆን ድጋፋቸውን በመስጠት ከእንግዲህ ወዲህ እንደድሮው አብረዋት በአለማዊው መድረክ የማይቆሙ መሆኑን ሲያውቁ የትካዜ መልክ ቢታይባቸውም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ  ቤተክርስቲያን አማኞች በመሆናችን ወደ አንቺ የምንመጣበት አንችን ፈልገን የምንመጣበት መልካም ቦታ ላይ ስለምናገኝሽ እንዳልራቅሽን በመገመት በደስታ ጥያቄሽን መልሠናል መልካሙን ሁሉ ይግጠምሽ ብለዋታል። በእለቱ በነበሩት ወጣት ዘማሪያን መካከል ዘማሪ ቸርነተ ሰናይ ዘማሪ ያሬድ እና የመዝሙር ዜማና የግጥም ደራሲዉ ሊቀ ትጉሃን መኩሪያ ጉግሳና ሰባኪ ቀሲስ ተስፋዬ መቆያ እንዲሁም ዲያቆን ቢኒያም እና ሌሎችም የተገኙ ሲሆን በምሽቱ የተገኙትን አርቲስቶች አመስግነዉ የዛሬዉ ዝግጅት በእናንተ የተዘጋጀ መሸኛ ነዉ።
እኛ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ደግሞ ለእህታችን ለዘማሪት አቦንሽ አድነዉ ኖቬምበር 21.2012 በ 845 ኖርዝ ሃዋርድ ስትሪት አሌክሳንድሪያ ቨርጅኒያ በመናደርገዉ ዝግጅት ላይ በምናዘጋጀዉ የአቀባበል ዝግጅት ላይ እንድትገኙልን እናሳስባለን። በእለቱ ታዋቂ ዘማሪያን ዘርፌ ከበደ፣ ቸርነት ሰናይና ሌሎችም እዉቅ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዘማሪያንና ታዋቂ ሰባኪያን እንዲሁም ህዝበ ክርስቲያኖች የሚገኙ መሆኑን ገልጸዉ ምሽቱን በምርቃት አክትምዋል።
ምንጭ ባዉዛ ጋዜጣ



20121019

የኢትዮጵያ ፓርላማ አባላትን "እግዚአብሔር ኢትዮጵያን በበረከቱ ይጎብኛት " መባሉ አሳቃቸው

የማክሰኞዉን  የፓርላማ ዉሎ አላየሁትም ነበር። ብቸኛው  የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ንግግራቸውን ሲጨርሱ "እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሀገራችንን በበረከት ይጎብኛት" በማለታቸው አፈ ጉባኤዉን አባ ዱላን ጨምሮ የፓርላማ አባላቱ እንደሳቁ የሚያሳየዉን ቪድዮ ሳይ  እጅጉን ነበር ያዘንኩት ግራም ተጋባው። የ እግዚአብሔር ስም መጠራቱ  እንዲህ የሚያስቅ ከሆነ  እነርሱ የሚያመልኩት ምን ይሆን? የ እኛ ሀገር መሪዎች ስልጣኔ ነት መስሏቸው ነው እንዳልል ያደጉ አገራት መሪዎች ከንግግር በኃላ እግዚአብሔር ሀገራችንን ይባርክ ብለው ሲናገሩ አንድም ቀን ሰው ሲስቅ አይቼ አላቅም። ታዲያ ምን የሚሉት ይሆን የ እኛ ሀገር መሪዎች እንዲህ ድዳቸው እስኪታይ መሳቃቸው ከምን የመነጨ ነው? እኔ ግን በማመን እግዚአብሔር ኢትዮጵያንን እና ህዝቦቻን ይባርክ እላለው አሜን እስቲ እናንተም ይሄንን ሺድዮ  ተመልከቱ

20120913

ድምጻዊት አቦነሽ አድነው ዘፈን አቁማ ዘማሪት መሆኗን አስታወቀች


"ባላገሩ" በተሰኘው አልበሟ የምትታወቀው ድምጻዊት አቦነሽ አድነው ሙዚቃ ማቆሟን እና ወደ ዘማሪነት መግባቷን ይፋ አደረገች::
ድምጻዊቷ ካሁን በኋላ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ስርዓት መሰረት እግዚአብሔርን አመሰግነዋለዉም ብላለች::
"ይህን ዉሳኔ ለመወሰን 5 ኣመታት ያህል ፈጅቶብኛል " ያለችው ድምጻዊቷ "ማታ ማታ ስዘፍን  ቃሉን እራብ ነበር ጠዋት ቤተክርስትያን ለቅዳሴ ባልደርስም ቃሉን ስመቼ ስመለስ ልቤን ያጸናልኝ ነበር " ካለች በኋላ "በአዲሱ አመት አሮጌዉ ማንነቴን ቀይሮ እዚህ በ ቤቱ እድገኝ እና ቆሜ እንድዘመር  እግዚአብሔር ስለረዳኝ አመሰግለዋለው "በማለት
 "አበረታኝ ክንድህ ጌታዬ
አበረታኝ ፍቅርህ አምላኬ
 በስምህ ድኛለው ፀጋህ
በማደሪያህ ሆኘ ስጠራህ "የሚለዉን የዘማሪ ዳግምዊን  መዝሙር ዘምራለች:: ቀሲስ መምህር ተስፋዬ መቆያ አያይዘው እንደተናገሩት የጠፉ ወገኖቻችን ተመልሰው ለጌታ ክበር እንዲዘመሩ ሁላችንም በፍቅር በአንድነት እንቁም የሚል መልክት አስተላልፈዋል::
የቀድሞዋን ድምጻዊት አቦነሽ አድነዉን ምስክርነት የሚያሳየዉን video ይመልከቱ


20120904

በጀርመን የሚገኝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ማህበር ካህናት አቡነ መርቆርዮስ ወደ መንበራቸው እንዲመለሱ ጠየቁ


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
በጀርመን ሀገር በሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ሥር ሆነን  በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የአደራ ቃል መሠረት በንጹሐን አባግዕ የተመሰሉ ምዕመናንን ተግተን በመጠበቅ ቤተ ክርስቲያንንም በማገልገል ላይ የምንገኝ የማኅበረ ካህናት የጋራ ያቋም መግለጫ።

በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስቅዱስ እናተን   ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ   የሐሥ ፡20፡28-30



መሪዋና አጽናኞዋ መንፈስቅዱስ የሆነችው ጥንታዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተለያዩ  ዘመናት ብዙ የፈተና ጊዜያትን ተቋቁማ በማለፍ ተወዳዳሪ የማይገኝላት ቤተ ክርስቲያን መሆኗ ለማንም የተሠወረ አይደለም ።
   ለምሳሌም ያህል፦ የዮዲትንና የግራኝን  የመከራ ዘመን ብቻ መጥቀሱ ከበቂ በላይ ነው ማለት ይቻላል ።ወደዝዝር ሁኔታው  ለመግባት አሁን አስፈላጊ ስላልሆነ እናልፈዋለን ። አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት የሰበሰቧት ቤተክርስቲያን  ባሳለፈችው የመከራ ዘመን ሁሉ አንዲት በመሆኗ ችግሩን በአንድነት መንፈስ ተቋቁማ  እስከ አሁን ድረስ ያለምንም ችግር ደርሳለች ።ይችን ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነች ቤተ ክርስቲያን ለማዳከም በየጊዜው  ከውስጥም ከውጭም ያልተጠነሰሰ ሴራ የለም በውጭ በኩል ስናይ የምዕራባውያኑ የዕምነት ድርጅቶች ወቅትና ጊዜን በመጠበቅ ልጆቿን ምእመናንን ከጉያዋ እየነጠቁ የነሱን ዕምነት እንደ ህጻናት ወተት ግቶ በማሳደግ በዚች ቤተ ክርስቲያን ላይ በጠላትነት እንዲነሱ ማሰለፍ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የሀገሪቱ መንግሥት በየጊዜው  በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ የሚያደርገው ጣልቃ ገብነት ቤተ ክርስቲያኗን እየጎዳት ይገኛል። የሩቁን ትተን የቅርቡን  ብቻ እንኳ ብናይ በደርግ ዘመነ መንግሥት በቅትታ የቤተ ክርስቲያኒቱን  እንቅስቃሴ የሚከታተል ከመንግስት ሥራ አስኪያጅ እየተመደበ የቆየ ቢሆንም ከደርግ ውድቀት በኋላ ሀገሪቱን በኃይል የተቆጣጠረው የኢህዴግ መንግሥት ደግሞ ከቀድሞ በከፋ ሁኔታ በቤተ ክርስቲያን ላይ ጫናውን ከባድ እንደ አደረገው በለፉት  ዓመታት በግልጽ ታይቷል አሁንም እየታየ ያለ ችግር ነው።ምክንያቱም ቤተክህነቱ የቤተ ክርስቲያኗ ሳይሆን የመንግሥት ተቋም እስኪመስል ድረስ በሰፊው እጁን አስገብቶ በመሥራት ቤተ ክርስቲያኗን ሲያምሳት ቆይቷል ።በዚህም ምክንያት ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን ድርጊት  እየተቃወሙ ህይወታቸው አልፏል።
በደርግ ዘመን የነበረው ማእበል በኢህዴግ ዘመን ሞገዱ በርትቶ ከፍ ብሎ ከቤተ ክርስቲያኗ  ጉልላት ላይ በመውጣት እሱ የፈለገውን ፓትርያርክ በማስቀመጥ ቤተ ክርስቲያኗን ደፈረ፤ አባቶችን በመከፋፈል ጣልቃ በመግባት ዓላማው እንዲሳካለት አደረገ፤  ይህም ሊሆን የቻለው ብጹአን አባቶች የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ለዚች ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ህልውና ቅድሚያ በመስጠት  በአንድነት  ሊቆሙ ባለመቻላቸው ነው።




በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይኖት ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ  በቅዱስ ሲኖዶስ ምላዓተ ጉባኤ የተመረጡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በመልካም ጤንነትና በህይወት እያሉ የመላ ሕዝበ ክርስቲያኑና ካህናቱ ድጋፍ ሳይለያቸው መንበራቸውን በኃይል እንዲለቁ  መደረጉ ሁሉም የሚያውቀው እውነት ነው። እንደተለመደው በፈቃዳቸው ነው የለቀቁት ተብሎ እንዳይዋሽ በወቅቱ ፓትርያርኩን ከስልጣናቸው አስገድደው ያወረዱት ጠቅላይ ሚንሥተር የነበሩት አቶ ታምራት ላይኔ ፓትርያርኩን ከመንበራቸው አውርደው ለቤተ ክርስቲያኗ መለያየት ምክንያት መሆናቼው እንደሚጸጽታቸው በዓለም መድረክ ላይ ቀርበው የተሠራውን  ስህተት አምነዋል ።
አቶ ታምራት ላይኔን መንፈስቅዱስ አፋቼውን ከፍቶ ፊታቸውን ጸፍቶ ያናገራቸው ጠቢቡ ሰሎሞን  ለሁሉም ጊዜ አለው ባለው መሠረት እውነትና ንጋት እያደር እንደሚባለው የአባቶቻችን አምላክ ይሄን በማድረጉ ሎቱ ስብሐት ብለን  እናመሰግነው አለን።  ምንም እንኳን ያለፈውን ነገር ለታሪክ ባለሟያዎች ብንተወውም ለማስታወስ ያህል መጥቀሱ ተገቢ ነው። ምክንያቱም አንድ ነገር መዘንጋት የለበትም ። ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ መንበሬን አለቅም ብለው በነበረበት ጊዜ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በአንድነት ከጎናቸው ቁመው ቢሆን ኑሮ  ዛሬ ላለንባት ለቤተ ክርስቲያኗ መከፋፈል ባልተደረሰም ነበር።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት በደነገጉለት ቀኖና ነው። ቀኖና ቤተ ክርስቲያኑ የሚያዘው አንድ ፓትርያርክ በኅይወት እያለ መንበሩን መልቀቅ እንደሌለበት የሚደነግገው አንቀጽ ተጥሶ በሕጋዊው ፓትርያርክ ላይ ህገ ወጡ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ 5ኛ ፓትርያርክ በመባል በመንበሩ ላይ እንዲቀመጡ ተደረገ የወያኔ መንግሥት የፈለገውን ዓላማ ለማሳካት ብሎ  ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ጥሶ  ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አፍርሶ  አቡነ ጳውሎስን በቅዱሱ መንበር ላይ ቢያስቀምጣቸውም በሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጭ የሚገኝ ሕዝበ ክርስቲን አንድ ቀን አባትነታቸውን ሳያምንባቸው ሃያ ዐመት ሙሉ በተቃውሞና በውግዘት  ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ከሀገር  ውጭ በስደት ሁኖ የቤተክርስቲያንን ሥራ በመሥራት  ላይ ካለው በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ጋርም ተወጋግዘዋል ውግዘቱም  ሳይፈታ የሰላምና የአንድነት ጉባኤ በሁለቱ ሲኖዶሶች መካከል የሽምግልና ሥራ እየሠራ በአለበት በዚህ ጊዜ ፤ምዕመናንና ምዕመናት ሁለቱም ሲኖዶሶች የቤተ ክርስቲያኗን አንድነት ከነገ ዛሬ ያስተካክላሉ ብለው በተስፋ ሲጠብቁ አቡነ ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየተዋል ።ይህም ማኅበረ ካኅናቱን እጅግ ያሳዘነ ዐቢይ ጉዳይ  መሆኑን ሳንገልጽ አናልፍም።ምክንያቱም በሕይወት እያሉ የተበላሸው ተስተካክሎ የተጣሰው ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ተመልሶ ሁሉም የቤተ ክርስቲያን ችግር በእርቀ ሰላም ተፈትቶ ቢሆን ኖሮ  ለሁሉም  ቀላል ይሆን ነበር ።
 ነገርግን ይህ ባለመሆኑ የገባያ ግርግር ለቀጣፊ ይመቸዋል እንደሚባለው ለቤተ ክርስቲያኗ አንድነት ከማሰብ እና ጸሎት ከማድረግ ይልቅ የዚች ቤተ ክርስቲያን ተለያይቶ መቅረት የሚያስደስታቸው በመለያየቷ ምክንያት የላይ ፈሪ የታች ፈሪ በማለት ከሁለቱም ክፍል ፍርፋሪ የሚለቅሙ የውስጥ ጠላቶች በየድህረገጹ ስለ ፓትርያርክ ምርጫ ሲያናፍሱ በመታየታቸው የቤተክርስቲያን መሥራች የሆነው አምላክ አበው ልብ ይስጣቸው እንላለን።
እስካሁን ቤተ ክርስቲያኗን ለሁለት የከፈለው ጉዳይ በራሱ በእግዚአብሔር ፈቃድ አንደኛው አባት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ስለዚህ አሁን በህይወት ያሉት ቀድሞም ያላግባብ በመንግሥት ኃይል ከሥልጣናቼው እንዲወገዱ የተደረጉት  አባት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ወደመንበራቼው ሊመለሱ ይገባል። ይህም ሊሆን የሚችለው ኢትዮጵያ የሚገኙት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ለቤተ ክርስቲያኗ አንድ መሆን በአድነትና በቅንነት ሲቆሙ ብቻ ነው።
ይህ ካልሆነ ግን ባለፉት ሃያ ዓመታት እንኳ የተለያዩ  ጥናቶች እንዳመለከቱት በቤተ ክርስቲያኗ መከፋፈል ምክንያት ወደ14 ሚሊዮን የሚጠጉ ምዕመናን ወደሌላ ቤተ ዕምነት እንደሄዱ ተረጋግጧል።
 ቅዱስ ሲኖዶስ ካለፈው ስህተት ተምሮ ለቤተ ክርስቲያንና ለምዕመናን አንድነት ሲል ቀኖናዉን መልሶ መጠበቅና ማስጠበቅ ይገባዋል እንላለን። ያለፈው ስህተት እናዳይደገም  በታሪካዊቷና ጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ የታሪክ ጠባሳ ለትውልዱ እንዳይተላለፍ ፤ትውልዱም በአባቶች ላይ እምነት እንዳያጣ በኢትዮጵያ ያሉ የቅዱስ ሲኖዶስን አባላት በቤተ ክርስቲያን አምላክ እያሳሰብን የሚከተለውን  ያቋም መግለጫ እናስተላልፋለን። 


  1. አሁን በስደት ላይ ያሉት አባት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በስቸኳይ ወደመንበራቸው እንዲመለሱ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በፍጹም ፍቅርና አንድነት የተጣለባችሁን መንፈሳዊ ግዴታ በመወጣት የቤተ ክርስቲያኒቱን ችግር ለአንድ ጊዜና ለመጨረሻ ጊዜ እንድታስወግዱ ፤ቤተ ክርስቲያንን እንድትጠብቋት መንፈስ ቅዱስ እናተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው እና ለራሳችሁ ልትጠነቀቁ ይገባል የሚለውን ቃል እንድትፈጽሙና ከታሪክ ተጠያቂነት እንድትድኑ። ይህ ባይሆን ግን በቤተ ክርስቲያኗ ላይ ከቀድሞ በከፋ ሁኔታ የልዩነት አድማሱ የእየሰፋ እልባት ወደማይገኝለት ችግር እየገባን እንደሆነ ከወዲሁ እንድታውቁ እና እንድታስቡበት እንጠይቃለን፤
  2. በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የተጋረጠው ችግር ሳይፈታ ለሹመት የሚሯሯጡትን የቤተ ክርስቲያንና የሀገር ጠላቶች በጽኑ እንቃወማለን፤
  3. የኢትዮጵያ  ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት፤ አባቶች ካኅናት፤ዲያቆናት፤የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች መላው ህዝበ ክርስቲያን የቤተ ክርስቲያን ቀኖና እደቀድሞው እንዲስተካከል ወደፊትም ተጠብቆ  እንዲኖር በጸሎትም በሀሳብም እድትረባረቡ በቤተ ክርስቲያኗ ስም እንሳስባለን፤
  4. መንግሥት እስካሁን በቤተ ክርስቲያኗ ላይ የሠራውን ስህተት አርሞ እጁን ከቤተ ክርስቲያኗ ላይ በማንሳት ለቤተ ክርስቲያኗ አንድነት የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፍና በስደት ያሉት ፓትርያርክ ወደመንበራቸው ተመልሰው መለያየት ተወግዶ ሁሉም ለአንዲት ኢትዮጵ በጋራ እንዲረባረብ እንቃፋት ከመሆን  እንዲታቀብ እንላላን፤
  5. በኢትዮጵያ የሚገኙ የፖለቲካና የኅሊና እሥረኞች ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው ተከብሮ ከሥር ተፈትተው እንደማንኛውም ኢትዮጵዊ ዜጋ በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ሀሳባቸውን በነጻነት  እንዲገልጹ እንጠይቃለን፤
  6. በአሁኑ ሰዓት አገሪቱን እየመራ ያለው መንግሥት ከመቼውም በላይ ለሰላም በመነሳት  እና ከተቀዋሚዎች ጋር በመስማማት ብሔራዊ እርቅ ሁኖ በሁሉም የተቃውሞ ጎራ ያሉት ወገኖች የሚሠሩት  ለሀገርና ለህዝብ እስከሆነ ድረስ እርቀ ሰላም እንዲመሠረቱና ሀገራችንን የሰላም ቀጠና በማድረግ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቻችሎና ተከባብሮ በመኖር አብሮ የመኖር እረዕያችን እውን እንዲሆን ፈቃደኝነትን እንዲያሳዩ ስንል እናሳስባለን።
በመጨረሻም ሁሉን በፈቃዱ ማድረግ የሚቻለው ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ያሉትን  የአባቶቻችን አንድነት እንዲያሳየን እንለምነው አለን ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፤
ነሐሴ 26 ቀን 2004 ዓ.ም
ጀርመን ፍራንክፈርት

20120820

የዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ምርጫ አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖደስ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ



ሕገ ቤተ ክርስቲያን ስለ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ

አንቀጽ 17
·              ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ
1.    ፓትርያርኩ በሞት ሲለይ ወይም በዚህ ሕግ አንቀጽ 16 መሠረት ከሥልጣኑ ሲወርድ ቅዱስ ሲኖዶስ በሹመት ቀደምትነት ካላቸው ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በዕለቱ ዐቃቤመንበረ ፓትርያርክ መርጦ ይሾማል፡፡ የተተኪው ፓትርያርክ ምርጫም ይካሔዳል፡፡
2.    የተተኪው ፓትርያርክ ምርጫ አፈጻጸም እንደጊዜውና እንደሥራው ሁኔታ እየታየ 40 እስከ 80 ቀን ባለው ጊዜ ይሆናል፡፡
3.    የዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ተግባር
ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ጊዜያዊ ጉደዮችን ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር እየመከረ ያከናውናል፡፡
በፓትርያርኩ ምርጫ ጊዜም የቅዱስ ሲኖዶስ ሊቀ መንበር ሆኖ ምርጫውን ያስፈጽማል፤ እርሱ ግን ከምርጫው አይገባም::

ምንጭ፦ ሕገ ቤተ ክርስቲያን 1991 .
.