20110215

ወለንኪ ቅዱስ ዮሓንስ ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በቃጠሎ ሙሉ ለሙሉ ስለመዉደሙ



ባለፈው አመት ጥር 2002 ዓ.ም ከ አስገራሚው እና ታሪክን በ ሰሩ ወጣቶች ተከብሮ ከዋለው የ ጥምቀት በዓል በኃላ የተሰማው አስደንጋጭና አሳዛኝ ዜና ነበር:: እሱም በምዕራብ ሽዋ ከ አዲስ አበባ 65 ኬ.ሜ እርቆ የሚገኘው የ ወለንኪ ቅዱስ ዮሓንስ ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ባልታወቁ ወገኖች ሙሉ ለሙሉ መቃጠል ነበር:: በቃጠሎው ከታቦቱ በስተቀር መላው ቤተ ክርስቲያኑና ንዋየ ቅዱሳት ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል::ይህም ድርጊት በከተማዋና በዙሪያዋ ብሎም በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የተዋህዶ ልጆች እና ሀገራቸዉን የሚወዱ ወገኖችን ያስቆጣ ነበር እኩይ ተግባር ነበር:: በአጭር ጊዜ ዉስጥ ቤተክርስቲያኑ ተሰርቶ ንዋያተ ቅዱሳት ተማልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምራል::አሁን ግን ያ ሁሉ አልፎ ቤተክርስቲያንዋ እንደገና አገልግሎት መስጠት ጀምራለች ሁሉን ያከናወነልን እግዚአብሔር ይመስገን:: "የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።" ማቴ 16:18 ግራኝ አህመድም ዮዲት ጉዲት ሁሉም ተዋህዶን ለማጥፋት ሞከሩ አልቻልሙም ይልቁንስ እየሞትን በዛን በመግደል ጽድቅ እንደሌለ በ እርግጥ አሳይተናል ለምሳሌ ፓዉሎስ አንገቱን ተሰየፈ ጴጥሮስም ተሰቀለ ብዙ ቅዱሳን በ ስቃይ እንዳለፉም እናዉቃለን የተዋህዶ ልጆች ዛሬም በ ስቃይ በፈተና ማለፍን ከ አባቶቻችን ተምረናል እና ቀዳሚ በሆነችው ተዋህዶ እንጽና ፍቅርን ያስተማረን የ እግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው እና ክፉን አትፍሩ

2 comments:

  1. የጠላት ሥራ ስለሆነ እስዋ ቤትዋን ከክፉ አድራጊዎች ልቦና ትስጣቸው መድሀኒያለም አጥፊዎችን ልባቸውን መልሰው

    ReplyDelete