20101016

በ እኛ ነዋየተ ቅዱሳን የመናፍቃን ጭፈራ

የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።

የማቴዎስ ወንጌል7፥15

ዛሬ ይህን ለመጻፍ ያስገደደኝ ትላንት አንድ ጋደኛዬ ኢትዮ ትዩብ በሚለው ድህረ ገጽ ላይ የወጣዉን ምስለ ድምጽ ( http://www.ethiotube.net/video/8669/Yetsidiq-Tsehay-Ethiopian-Gospel-Singers%EF%BB%BF ) መናፍቅኑ ከዚህ በፊት በ ቅድስት ቤተክርስትያናችን ላይ ያልሆኑ ስብከቶችን እና የ እኛ የ ሆኑ የዘማ እቃዎችን በመጠቀም ሲዘፍኑ አይተናል በዚም አላበቁም ከ 4 እና 5 አመታት በፊት ዉዳሴማሪያምን ቀየር አድርገዉ ዘመን ባፈራዉ የድምጽ መሳሪያ በመጠቀምን ሲዘፍኑም አይተን አልፈናል የቅርብ ጊዘዉን ላስታዉሳቹ አንድ በልመና የሚተዳደር ሰዉን በገንዘብ ይሁን በሃይ በማስፈራራት አቡነ ያሬድ ነኝ ብሎ የሃሰትምስክርነት እንዲሰጥ ተደገ ይህንንም በዝምታ አለፍን.ለ ኢትዮጲያ ድህነት ተጠያቂዎ የ ኦርቶዶክስ በተክርስትያን ናት ሲሉም አድምጠን አልፈናል

እዚህ ላይ ሳልጠቅስ ማለፍ የማልፈልገዉ ነገር የ መምህር ዘበነን እዉነትን የማዉጣት ስራ ሊበረታታ ይገባዋል . የ ሃይማኖት መሪዎቻችንም በዚህ ነገር ላይ መላ ቢሉ ጥሩ ነው እላለው

ይሄን ቪድዮ ከሌላዉ ለየት የሚያደርገዉ የከበሮዉ፣ የፀናጽሉ፤ የመቋሚያው አላንስ ብሎ መፆረ መስቀሉን፣ጽናውን፣ ቃጭሉን ይዘዉ ሲጨፍሩ አየን ይህንንስ በዝምታ ማለፍ ያለብን አይመስ ለኝም. አባቶቻችን ያቆይልንን የዜማ መሳሪያዎችን እና ንዋያተ ቅዱሳቱን ይዘው ሲጨፍሩ ዝም ካልን የሚቀትለዉ ታቦትን ይዘዉ ይሆናል የሚጨፍሩት.

የቀደሙት አባትኦቻችን ያቆዩልንን ኦርቶዶስ ተዋህዶን እኛም ከ የዜማ መሳሪያዎቻቻን እና ንዋያተ ቅድሳቱ ከሙሉ ሚስጥርና ትርጉማቸው ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፉ የእኛ ሀላፊነት ነው።

ተኩላዉ ለምድ ለብሶ በርግጥ መጣል እና

አምላክ ሆይ አድነን ፍጠን ተሎ ና

1 comment: